Thursday, October 8, 2015

ዚቅ ወመዝሙር አመ ፴ ለመስከረም

  
 እንኳን ለዘመነ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ በቤተክርስቲያናችን ዘመነ ጽጌን እና የእመቤታችንን ስደት አስመልክቶ ለሚቀጥሉት 6 እሑዶች (መስከረም ፴ ጥቅምት፯ ጥቅምት፲፬ ጥቅምት፳፩ ጥቅምት፳፰ ኅዳር፭) የሚቆመውን የማኅሌተ ጽጌ ዚቅና መዝሙር በየሳምንቱ ይዘንላችሁ እንቀርባለን::




ነግሥ ለኵልያቲክሙ...ዚቅ

ወኃይዝተ ወንጌል የዓውዳ ለቤተክርስቲያን፤
እም አርባዕቱ አፍላጋት፤
እንተ ትሰቀይ ትእምርተ ለለጽባሑ፤
እማቴዎስ ልደቶ ወእማርቆስ መንክራቶ፤
እም ሉቃስ ዜናዊ ተሰምዮ ወእም ዮሐንስ በግዓ፤
ወዘንተ ሰሚዓ ትገብር በዓለ በፍግዓ፤

ማኅሌተ ጽጌ

ጽጌ አስተርአየ ሠሪፆ እምዐፅሙ፤
ለዘአማኃኪ ጽጌ ለገብርኤል በይነ ሰላሙ፤
ወበእንተዝ ማርያም ሶበ ሐወዘኒ መዓዛ ጣዕሙ፤
ለተአምርኪ አኀሊ እሙ ማኅሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፤

Friday, September 25, 2015

መርገምን በመስቀል ላይ ሻረ

  በቅmeskel dameraድሚያ ከዘመን ወደ ዘመን ያሸጋገረን ለብርሃነ መስቀሉ ያደረሰን በሀብቱ የሳበን በረድኤቱም ያቀረበን አምላካችን ልዑል እግዚአብሔር የተመሰገነ ይሁን፡፡

ከላይ በርዕሱ ያነሣነው ኃይለ ቃል ቅዱስ አትናቴዎስ የመስቀሉን ነገር በተናገረበት ድርሳኑ የተናገረው ነው፡፡ አስተሀፈረ ኃጢአተ በዲበ ምድር ወሰአረ መርገመ በዲበ ዕፀ መስቀል ወአብጠለ ሞተ በውስተ ሲዖል ወነሰተ ሙስና እምውስተ መቃብር”

“በምድር ላይ ኃጢአትን አሳፈረ መርገምን በመስቀል ላይ ሻረ ሞተ ነፍስን በሲዖል አጠፋ ፈርሶ በስብሶ መቅረትን በመቃብር አፈራረሰ” በማለት ጌታችን ለሰው ልጆች ነጻነት እና ድኅነት የከፈለውን የቤዛነት ሥራ በተናገረበት ክፍል የተናገረው ነው የሰው ልጆች ነጻነታቸው የተዋጀው በመስቀል ተሰቅሎ ቅድስት ነፍሱን ከቅድስት ሥጋው በሥልጣኑ ለይቶ ዲያብሎስን በመስቀሉ ገሎ ሥጋውን ቆርሶ ደሙን አፍሶ በአካለ ነፍስ ወደ ሲዖል ወርዶ ነፍሳትን ከዲያብሎስ ባርነት ከአጋንንት ቁራኝነት ከሲዖል ግዛት ነጻ አውጥቷቸዋልና፡፡

Wednesday, September 23, 2015

ተቀጸል ጽጌ- የዐፄ መስቀል


 ተቀጸል ጽጌ ማለት የአበባ በዓል ማለት ነው፡፡ ክረምቱ፣ ድጡ፣ ማጡ፣ ችግሩና ጨለማው ተወግዶ ምድር በልምላሜ የምታሸበርቅበት፣ በአበባ የምትደምቅበት ወቅት በመሆኑተቀጸል ጽጌ እየተባለ ይከበራል፡፡የተቀጸል ጽጌ በዓል የተጀመረው በ6ኛው ምዕተ ዓመት በዐፄ ገብረ መስቀል አማካይነት ሲሆን በዓሉ የሚከበረው የክረምቱ ማብቃት የሚያበስሩ አበቦች በሚፈኩበት ወር በመስከረም 25 ቀን ለንጉሡ የአበባ ጉንጉን /አክሊል/ በማበርከት ነበር፡፡

Friday, August 14, 2015

የጩጊ ማርያም ገዳም ታሪክ

     

የጩጊ ማርያም አንድነት ገዳም ሰሜን ጎንደር ሀገረስብከት በወገራ ወረዳ ከሚገኙ ገዳማት አንዱ ነው፡፡ገዳሙ ከጎንደር ከተማ 25 ኪ.ሜ ርቀት ላይ ኮሶዬ ከተማ ሲደርሱ ሶስት ሰአት የእግር መንገድ እንደተጓዙ የሚገኝ ገዳም ነው፡፡
የጩጊ ማርያም ገዳም በ17ኛው መቶ ክፍለ ዘመን የተመሰረተ ጥንታዊ ገዳም ሲሆን የመሰረቱትም አባ ምእመነ ድንግል የተባሉ ጻድቅ ናቸው፡፡ገዳሙም ጻድቁ የጸለዩበት እና ከጌታችን ከመድሃኒታች ከኢየሱስ ክርስቶስ ቃልኪዳን የተቀበሉበት ቅዱስ ቦታ ነው፡፡
የአባ ምእመነ ድንግል ታሪክ
አባ ምእመነ ድንግል የተወለዱት በወገራ አውራጃ ሲሆን ገና በህፃንነታቸው በእናት በአባታቸው ቤት እያሉ ጀምሮ መንፈሳዊ ትሩፋቶችን በመስራት በታላቅ ተጋድሎ ኖረዋል፡፡ አባታችን ምእመነ ድንግል የምንኩስና ልብስና የእግዚአብሔር ጸጋ በመፈለግ አዳጋት ማርያም ወደ ምትባል ገዳም በመሄድ ብዙ ተጋድለዋል፡፡ ከዚያም ወደ ዋልድባ ገዳም በመሄድ ብዙ ተጋድለዋል፤ጽናታችውን ያዩ የዋልድባ ገዳም መነኮሳት አባትና መምህር እንዲሆኗቸው ቢጠይቋቸው እራሳቸውን ዝቅ በማድረግ “እኔ መምህርና አባት ልሆን አይገባኝም ” በማለት እንቢ ቢሉም መነኮሳቱ አበምኔት አድርገው ሾመዋቸዋል፡፡ አባታችንም በተሾሙበት በዚህ ገዳም በከፍተኛ ተጋድሎና በእግዚአብሔር ጸጋ ብዙ መንፈሳዊ መነኮሳትንና መምህራንን በትምህርታቸው አፍርተዋል፡፡

Tuesday, August 4, 2015

ጾመ ፍልሰታ ለቤተ ክርስቲያን ሰላም


ኢትዮጵያ የእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የአሥራት አገር ናት፡፡ ሊቃውንትም ነቢያት የተነበዩትን ትንቢት የቆጠሩትን ሱባዔ መሠረት በማድረግ ቅድስት ድንግል ማርያም በኪደተ እግሯ ኢትዮጵያን መባረኳን ያስተምራሉ፡፡ «ነቢዩ ዕንባቆም የኢትዮጵያ ድኳኖች ሲጨነቁ ዐየሁ፤» ዕንባ. 37 ብሎ የተናገረው ቃለ ትንቢት እመቤታችን የኢትዮጵያን አውራጃዎች ለመባረኳ ማስረጃ መሆኑን ሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን ይተረጉማሉ፤ ያመሠጥራሉ፡፡
 
ኢየሱስ ክርስቶስ ኢትዮጵያን ለእናቱ አሥራት አድርጐ በመሥጠቱ በእርሷ በኩል ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሆን የነገረ ድኅነት ምሥጢር በመከናወኑ ኢትዮጵያውያን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተለየ ፍቅር አለን፡፡ የአብነት /የቆሎ/ ተማሪዎች በትምህርት ዓለም ከአንዱ ወደሌላው እየተዘዋወሩ /የአብነት/ ትምህርት ሲማሩ በእንተ ስማ ለማርያም፤ ስለማርያም እያሉ፡፡ የእመቤታችን ስም ስንቅ ምግብ ሆኗቸው ይጠቀሙበታል፡፡ ግሼን ደብረ ከርቤ የልጇ ግማደ መስቀል ከከተመበት አምባም የሚጓዙ ምእመናን «አንድ እፍኝ ሽምብራ አልያዝኩም ከቤቴ ስሟ ስንቅ ነው የእመቤቴ» እያሉ በፍቅሯ ተማርከው ግብር ሰፍረው ዕጣን ቋጥረው ሱባዔ እየገቡ ይማፀኗታል፡፡

Saturday, July 11, 2015



ሰማዕተ ጽድቅ ቅዱስ ጴጥሮስ ወጳውሎስ

  እነዚህ ሁለት ቅዱሳን አባቶቻችን የቅድስት ቤተክርስቲያናችን አዕማድ ናቸው፡፡ በመሠረትነት በአጸኗት ቤተክርስቲያን ያላቸው የክብር ሥፍራ ላቅ
ያለ ነው፡፡ ይህ የሆነው እንዲሁ አይደለም፡፡ ለቤተክርስቲያንና
በቤተክርስቲያን የፈጸሙት አገልግሎት በዚህም የተቀበሉት ሰማዕትነት
ነው፡፡ ቅዱሳት መጻሕፍትም ይህን መልካም የሆነውን ታሪካቸውን ለእኛ
አርአያነት በሚሆን መልኩ ከትበውልናል፡፡ እኛም ለአርአርያነት በሚሆን
መልኩ የእነዚህን ደጋግ ሁለት ቅዱሳን አባቶች ታሪክ፣ ዕውቀትና
መንፈሳዊ አገልግሎታቸውን ከዚህ በመቀጠል አቅርበናል፡፡
1. ሁለቱ ሐዋርያት ሲጠሩ የነበሩበት ሕይወት
ሐዋርያው ቅዱስ ጴጥሮስ በገሊላ ባሕር ዳር በምትገኘው በቤተ ሳይዳ
ሲወለድ ሐዋርያው ቅዱስ ጳዉሎስ ደግሞ በጠርሴስ ከተማ ተወለደ፡፡

Tuesday, June 30, 2015

ጸሎተ ፍትሐት ምንድ ነው? ለምንስ ይጠቅማል?
 

 
ሰኔ 23 ቀን 2007 ዓ.ም.
ፍትሐት ማለት ከዚህ ዓለም በሞት ለሚለዩ ሰዎች በሕይወተ ሥጋ ሳሉ ከሠሩትና ከፈጸሙት በደል እንዲነጹ ከማእሠረ ኃጢአት እንዲፈቱ ወደ እግዚአብሔር የሚቀብ ጸሎት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለሙታን ጸሎተ ፍትሐት እንዲደረግ ታዝዛለች፡፡
ጸሎተ ፍትሐት ለበደሉት ሥርየት ኃጢአትን፣ ይቅርታን ዕረፍተ ነፍስን ያሰጣል፡፡ ለደጋጎች ደግሞ ክብርን፣ ተድላን፣ ዕረፍትን ያስገኛል፡፡

Friday, May 29, 2015

                                የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ አትጥራ!

የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ መጥራት ሲባል ምን ማለት ነው? የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የከበረ በመሆኑ እንደተገኘ የሚጠሩት፣ እንደአጋጠመ የሚናገሩት አይደለም፡፡ ይልቁንም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ በትሕትና ሆነው ሊጠሩት የሚገባ ክቡር ስም ነው፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስም ያለአግባብ በነገራቸው ሁሉ ውስጥ ሲያስገቡት፣ ሥፍራም ጊዜም ሳይመርጡ እንደፈለጉት ሲጠሩት ይስተዋላሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች እምነትና ፊሪሃ እግዚአብሔር አላቸው ለማለት አያስደፍርም፤ ምክንያቱም የሚያምኑና
 
ከዚህ ቀጥለን ሰዎች ስሙን በከንቱ የሚጠሩባቸውን ሁኔታዎች ባጭር ባጭሩ ለመመልከት እንሞክራለን፡፡

Tuesday, May 26, 2015


                                      ተዋሕዶ-በደም


በደም ተመሥርተሽ
በደም ተገንብተሸ
በደም ተዋሕደሽ
በደም ተሰራጭተሸ

Wednesday, May 20, 2015

ዕርገተ ክርስቶስ

ግንቦት12ቀን 2007ዓ.ም
በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ
አልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለመሕያው ዮሐ.3፥13
Ereget
ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ይህ ኃይለ ቃል ክብር ምስጋና ይግባውና ስለጌታችን፣ አምላካችን፣ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት መውረድ ከድንግል ማርያም መወለድ እና የሰውነቱን ሥራ ጨርሶ በክብር ወደ ሰማይ ማረጉን የሚገልጽ ነው፡፡ እንደሚታወቀው አምላካችን ስለሁለት ዐቢይ ጉዳዮች ሰው ሆኗል፡፡

Sunday, May 17, 2015

ዋዜማ ዘግንቦት ያሬድ


ዋዜማ
ንዑ ንትፈሣሕ በመኃልዪሁ ወንንግር ለካህን ውዳሴሁ፤
ከመ ሱራፌል ለያሬድ ክላሑ ለክርስቶስ ሰበከ ትንሳኤሁ፤
ማሕበረነ ይባርክ በእዴሁ፤
ምልጣን
ከመ ሱራፌል ለያሬድ ክላሑ ለክርስቶስ ሰበከ ትንሳኤሁ፤
ማሕበረነ ይባርክ በእዴሁ፤
ሃሌ ሉያ ንዑ ንትፈሣሕ በመኃልዪሁ ወንንግር ለካህን ውዳሴሁ፣
ያሬድ ጸሊ በእነቲአነ ጸሎትከ ወትረ ይብጽሐነ፤
ያሬድ ጸሊ በእንቲአነ፤
ያሬድ ማኅሌታይ ለእግዚአብሔር ካህኑ፤
ስብሐተ ትንሳኤ ዘይዜኑ፤
ኦሪት ቶታኑ ወወንጌል አሳእኑ፤
ትርድአነ ነአ በህየ መካኑ፤
ከመ ጸበል ግሑሳነ ጸርነ ይኩኑ፤
እለሰ ይዌድሱ ትንሳኤሁ ወይቄድሱ፣
ያሬድ ካህን ምስሌሆሙ ያንሶሱ፤
ሰላም
አንበሳ ዘሞአ ፍጹም ውእቱ፤
እምስርወ ዳዊት ወፈትሐ፤
መጽሐፈ ትምህርት፤
ያሬድ የሐሊ ትንሳኤሁ፤
ወለብሰ ሰላመ ዚአሁ፤

ዚቅ ዘግንቦት ያሬድ ዘይትበሃል በደብረ ይባቤ


ነግሥ
ሰላም ለአብ ገባሬ ኵሉ ዓለም፤
ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም፤
ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም፤
ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም፤
ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም፤

ዚቅ
አብኒ የሐዩ ዘፈቀደ፤
ወልድኒ የሐዩ ዘፈቀደ፤
መንፈስቅዱስኒ የሐዩ ዘፈቀደ፤
እስመ በፈቃዱ ወለደነ በቃለ ጽድቁ፤
ወበተስፋ እንተ ባቲ ነሐዩ፤
እንተ ኪያሃ ይጸንሁ ጻድቃን፤
ሰላም ለቆምከ ጽዱለ ዋካ ወሞገስ
ሀበ መቃብሩ ዘቆመ ለበኵረ ትንሣኤ ክርስቶስ
ሚካኤል ሰዋኢ በግዐ ትንሣኤ ሠላስ፤
ኢይልሕቅ ወርኃ ምግብየ ከመ ሕዝቅያስ ንጉሥ፤
ፀሐየ ሕይወትየ አቅም በማዕረር ሐዲስ፤
ዚቅ
ቀዊሞ ገሐደ ውስተ አውደ ስምዕ፤
ያሬድ ሰበከ ትንሳኤ ሞቱ ለበግዕ፤
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤
ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤
መሰረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤
ኪያኪ ሰናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤
እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኰት ስሙ፤
ዚቅ
ትውልደ ትውልድ ያስተበጽዕዋ፤
መላእክት በሰማያት እኅትነ ይብልዋ፤
ፍሬ ማኅፀና ለማርያም ቤዘወ ፄዋ፤
ወአግብኦሙ ውስተ ርስቶሙ ለአዳም ወለሔዋ፤
ሰላም ዕብል ለያሬድ ቀሲስ፤
ለኢትዮጵያ ነደቃ በሃሌ ሉያ ምድራስ፤
አስተካልሐ በውዳሴ በዜማ ሠላስ፤
በመሐልይሁ ሐዋዝ ወስብሐት ሐዲስ፤

Monday, May 11, 2015

የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠናቀቀ



ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም.
ሚያዝያ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በጸሎት የተጀመረው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲካሔድ ቆይቶ  ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ረፋድ ላይ ተጠናቅቆ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

Thursday, May 7, 2015

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ያስገነባው መንበረ ጵጵስና እና ጽ/ቤት ተመረቀ


001deb002deb
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገነባው ለመንበረ ጵጵስና እና ለጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል ባለ ሁለት ፎቅ ሕንፃ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሚያዝያ 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመረቀ፡፡

Wednesday, May 6, 2015

ስለትያትርና ኪነጥበብ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እነዳስተማረው

ከአቤል ተስፋዬ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
…እንግዲህ (አብዝታችሁ) ብታነቡ የጌታችን ተከታይ ሆናችኋል፡፡ እርሱም ያነባ (ያለቅስ) ነበርና፤ በአልአዛር (መቃብር ላይ)፤ በከተማይቱ (ኢየሩሳሌምን) ላይ፤ ይሁዳም ባገኘው ጊዜ አብዝቶ አዝኖ ነበር፡፡ ብዙዎች ሲያዝን አይተውታል ነገር ግን ሲስቅም ሆነ ፈገግ ሲል ለቅጽበት ስንኳ በየትኛውም ጊዜ ያየው አንዳችም የለም፤ ከወንጌላውያኑ የትኛቸውም ይህን እንዳደረገ አልገለጹም፡፡ (ቅ.) ጳውሎስንም እንዲሁ፤ እንዳለቀሰ፤ ለሶስት አመታት ቀን ከሌሊት (ያለመቋረጥ) እንዳነባ ራሱም ገልጿል፤ ሌሎችም ስለርሱ ይህን መስክረዋል፤ እንደሳቀ ግን እርሱም የትም ቦታ ላይ አልጠቀሰም ከሌሎች ቅዱሳንም መካከል ይህን እንዳደረገ የተገለጸ ማንም የለም፤ ስለ ሳራ (የአብርሀም ሚስት) (እንደሳቀች) ተጠቅሷል ይኸውም (በሦስቱ መላዕክት) በተገሰጸችበት ወቅት ነበር፤ እንዲሁም የኖኸ ልጅ በተመሳሳይ ስለመሳቁ ተጽፏል፤ ይህን ባደረገበት ወቅት ግን (በአባቱ ተረግሟልና) ነጻነቱን በባርነት ለወጠ፡፡

እንዲህ የምላችሁ ሳቅ (ጨዋታ) የተባለን ሁሉ ለመኮነን አይደለም፤ አእምሯችሁ በከንቱነት እንዳይጠመድ ለማቀብ ነው እንጂ፤ እስኪ ልጠይቃችሁ በምቾት የምትንደላቀቁና በከንቱነት የተዘፈቃችሁ ሆናችሁ ሳለ በሚያስፈራው (የጌታችን) የፍርድ መንበር ፊት ቆማችሁ እዚህ (በምድር) ላይ ሳላችሁ ስለሰራችሁት ነገር አንድ በአንድ አትጠየቁምን? በእርግጥ እንጂ… ምክንያቱም አውቀን በድፍረት ስለሰራነውም ሆነ ከአቅማችን በላይ ሆኖብን ስለበደልነው በደል ምላሽ እንድንሰጥ እንጠየቃለንና… ‹‹ በሰዎች ፊት የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ (በሰማዩ) አባቴ ፊት እክደዋለሁ›› ይላልና ጌታ፡፡ አለጥርጥር ማናችንም ጌታን ወደን አንክደውምና አውቀንና ፈቅደን አናደርገውም፤ ነገር ግን ይህም ቢሆን ከቅጣት አያድነንምና ይህንንም አስመልክቶ መልስ መስጠት ይኖርብናል፤ አውቀን ስለሰራነው ብቻ ሳይሆን ሳናውቅ የበደልነውም ጭምር ያስጠይቀናል፡፡ ‹‹ በራሴ አንዳች አላውቅም፤ ነገር ግን ይህ ምክንያት ሆኖኝ ከፍርድ አላመልጥም (አልድንም)›› ይላልና 1 ቆሮ 4፡4 ፤ደግሞም በሌላ ስፍራ እንዲህ ይላል ‹‹ ለእግዚአብሔር ቀናኢነት ያላቸው ናቸውና ይህን ቆጥሬላቸዋለሁ፤ ነገር ግን በእውቀት አይደለም›› ይሁን እንጂ ይህ በቂ ምክንያት ሆኖ አልተገኘም፡፡ ወደ ቆሮንጦስ ሰዎች በጻፈበት ወቅትም ደግሞ (ሐዋ. ቅ. ጳውሎስ) እንዲህ ብሏል ‹‹ እባቡ ሔዋንን በረቂቅ ተንኮሉ እንዳሳታት ሁሉ በጌታችን ካለ ቅንነት አእምሯችሁን እንዳይበርዘው እፈራለሁ››

Thursday, April 30, 2015

ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳፫



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አምላክ አመ ዕሥራ ወሠሉሱ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለተ ኮነ ፍጻሜ ስምዑ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዐቢይ ወክቡር ዘተሰምየ ፀሐየ ወኮከበ ጽባሕ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሚያዝያ ሃያ ሦስት በዚች ቀን ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ ሆነ፡፡

የዚህም ቅዱስ አባቱ መስፍን ነው፡፡ ስሙም አንስጣስዮስ ይባላል፡፡ ከቀጰዶቅያ አገር ነው፡፡ የእናቱም ስም ቴዎብስታ ይባላል ከፍልስጥዔም አገር ናት ታናሽ ሆኖ ሳለ አባቱ ዐረፈ፡፡



ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሔደ፡፡ ንጉሡም ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው፡፡

ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች፣ ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው፡፡

ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ፡፡ ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም፡፡

በሊቢያ በአይ ኤስ አይ ኤስ ስለተሰዉ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች የአኀት አብያተ ክርስቲያናት አባቶች መልዕክት

€œለገዳዮቹ ጸልዩ፤ ይቅርም በሏቸው፡፡€ /ብጹዕ አቡነ አንጄሎስ በኮፕት ኦርቶዶክስ የታላቋ ብርቲያንያ ሊቀ ጳጳስ/

001abune angeloአሸባሪው አይ ኤስ አይ ኤስ 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን መግደሉንና ለዚህም ሓላፊነቱን መውሰዱን ተናግሯል፡፡ ክርስቲያኖቹን በመግደሉ ይቅር እንለዋለን፤ እንጸልይለታለንም፡፡ በማለት ብፁዕ አቡነ አንጄሎስ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላላፈዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ አንጄሎስ አሸባሪው ቡድን በፈጸመው ድርጊት የተሰማቸውን ሐዘን ሲገልጹም €œአይ ኤስ አይ ኤስ በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ ክርስቲያኖቹን ሲሰዋቸው የሚያሳያውን ምስል ወድምጽ በሁለት ቅጂ በኢንተርኔት ለቋል፡፡ በለቀቀው ምስል ወድምጽም 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ተገድለዋል፡፡

Thursday, April 23, 2015

ሰማዕታቱ እና ሰማዕትነት




ሰማዕት የሚለው ቃል ከግዕዙ “ሰምዐ” ካለው የወጣ ነው፡፡ትርጉሙም መሰከረ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሰማዕት ላለው ቃል መነሻው ምስክር ማለት ነው፡፡“በኢየሩሳሌም ፣ በይሁዳ ፣በሰማርያ እሰከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” ሐዋ 1፥8-22 እንዳለው፡፡ እንግዲህ ምስክር የሚለው ቃል በመጀመሪያ ለሐዋርያት የተሰጠ ስም ሲሆን በኋላም ሀይማኖታቸውን እንደ ሐዋርያት ለሚገልጡ ምእመናን የተሰጠ ስያሜ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ደግሞ ምስክርነታቸውን የገለጡት በማስተማር ብቻ ሳይሆን ስለሚያስተምሩት ትምህርት(ወንጌል) ትክክለኛነት በፈቃዳቸው ሰማዕት እስከመሆን ደርሰው ነው፡፡ስለዚህ ሰማዕትነት ማለት ስለሃይማኖት ሲባል በፈቃድ ሞትን(መከራን) መቀበል ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ሰማዕትነት ሶስት ነገሮችን የያዘ ነው፡፡

Monday, April 20, 2015


ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ መግለጫ ሰጠ
                   
ሚያዚያ 12/2007
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሊቢያ በአሸባሪው አይሲስ እጅ በሰማዕትነት የተሠውትን ኢትዮጵያውያን በተመለከተ ዛሬ ጠዋት 5፡30 ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ከውጭ ሀገር ጉዞ ቀርተው በመንበረ ፓትርያርኩ የቅዱስ ሲኖዶሱን መግለጫ የሰጡ ሲሆን ሌሎች የእምነት ተቋማትም ተመሳሳይ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
መግለጫውን ተመልከቱት፡፡
  ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዐረፉ           
002abune peteros 
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የባሕር ዳር፤ የአዊና የመተከል አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ሚያዝያ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ጠዋት ዐርፈዋል፡፡

ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. በባሕር ዳር ከተማ የተገነባውን መንፈሳዊ ኮሌጅ በቅዱስ ፓትርያርኩ ካስመረቁ በኋላ ድንገት በመታመማቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደው ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆይም ሚያዝያ 10 ቀን ጠዋት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ሥርዐተ ቀብራቸው እሁድ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

Wednesday, April 15, 2015

የትንሣኤው ትርጉምና የሰሙነ ፋሲካ ዕለታት

                     ትንሣኤ የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡

             መገኛ ቃሉም ተንሥአ =  ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡
ትንሣኤ ማለት = መነሣት፣ አነሣሥ፤ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡ ትንሣኤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም አምስት ክፍሎች አሉት፡፡
አንደኛው ትንሣኤ ኅሊና ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡
ሁለተኛውም ትንሣኤ ልቡና ነው፡፡ የዚህም ምስጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡
ሦስተኛው ትንሣኤ ለጊዜው የሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል፡፡
አራተኛውትንሣኤ የክርስቶስ በገዛ የባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ የትምህርታችንም መሠረት ይኸው ነው፡፡
ዐምስተኛውና የመጨረሻው የትንሣኤ ደረጃም የባሕርይ አምላክ የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ መሠረት ያደረገ ትንሣኤ ዘጉባኤ ነው፡፡ ይህም ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ሁሉ እንደየሥራው ለክብርና ለውርደት፣ ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ይሆናል፡፡

Wednesday, April 8, 2015

በሰሙነ ሕማማት የሚነሡ ጥያቄዎችና መልሶቻቸውአትምኢሜይል
መጋቢት 29 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓዋጅ ከሚጾሙት አጽዋማት መካከል ዐቢይ ጾም፤ ጾመ ኢየሱስ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ አሁን በጾሙ መጨረሻ ሳምንት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕማምና ሥቃይ እንዲሁም እንግልት በምናስብበትና የጨለማውን ዘመን በምናስታውስበት ጊዜ /ሰሙነ ሕማማት/ ላይ እንገኛለን፡፡

ስለ ሰሙነ ሕማማት ስናነሣ በምእመናን ዘንድ የሚነሡ አንዳንድ ጥያቄዎች አሉ፡፡ እኛም እነዚህን ጥያቄዎች ለሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በማቅረብ የሰጡንን ምላሽ ይዘን ቀርበናል፡፡

Saturday, April 4, 2015

፰ተኛ ሳምንት ሆሳዕና በቅዳሴ ጊዜ የሚደረግ ሥርዓተ አምልኮ





በዋናው ዲያቆን                  ዕብ    9 ÷11  
በረዳቱ ዲያቆን                   1ጴጥ   4÷1-12
በረዳቱ ቄስ                       የሐዋ   28÷11-22
ምስባክ፡-


እምአፈ ደቂቅ ወሕፃናት አስተዳሎከ ስብሐተ፤
በእንተ ጸላኢ፤
ከመትንስቶ ለጸላኢ ወለገፋኢ፡፡    መዝ 8 ÷2


ትርጉም፡-                               
ከሕፃናት አንደበት ምስጋናን አዘጋጀህ፤
ስለጠላት ብለህ፤
ጠላትና ቂመኛን ታጠፋ ዘንድ፡፡


ወንጌል፡-                    ዮሐ   5 ÷ 11-13
ቅዳሴ፡-                     ዘጎርጎርዮስ

ሰሙነ ሕማማት



        የሰሙነ ሕማማት ሃይማኖታዊና ቱፊታዊ ክንዋኔዎች

በዐቢይ ጾም ከሰርክ ሆሳዕና ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡ በእነዚህ ዕለታት ውስጥ የተለያዩ ትውፊታዊ እና ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች አሉ፡፡ ከነዚህ ክንዋኖዎች ውስጥ አለመሳሳም፣ አክፍሎት፣ ቄጤማ ማሰር፣ ጥብጠባ፣ ጉልባን እና ሕፅበተ እግር ይገኙበታል፡፡ ስለእነዚህ ክንዋኔዎች በቅድስት ቤተ ክስቲያን ስላለው ትውፊታዊ አፈፃፀም መዛግብት አገላብጠን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡
አለመሳሳም፡- በሰሙነ ሕማማት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች መስቀል እንደማይሳለሙት ሁሉ መጨባበጥ፣ መሳሳምን የትክሻ ሰላምታ መለዋወጥን አይፈጽሙም፡፡ ሰላምታ የማንለዋወጥበት ምክንያት አይሁድ ጌታን ለመስቀል ሰኞ እና ማግሰኞ መከሩ አልሰመረላቸውም፡፡ ምክረቸው የተፈጸመው ረቡዕ ነው፡፡ ስለዚህ አይሁድ እያንሾካሾኩ እንሰቀለው ፤እንግለው ብለው ይማከሩ ነበር፡፡ በዘመነ ፍዳ ወቅት ሠላምና ፍቅር አለመኖሩን የሚገልፅልን በመሆኑ ያንን ለማስታወስ ስላምታ አንለዋወጥም፡፡ መስቀልም አንሳለምም፡፡ ሳምንቱ የክፋት ምክር የተመከረበት እንጂ የፍቅርና የደስታ ሳምንት የታየበት ባለመሆኑ ይህንን በማሰብ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡ አይሁዳ ጌታን በጠላቶቹ ለማስያዝ እኔ የምስመው እርሱ ነው ያዙት ብሎ በሰላምታው ምልክት ሰጣቸው ይህ ሰላምታ አምሐ ቅድሳት አይደለም ተንኮል የተሞለበት እንጂ፡፡ የዲያቢሎስም ሰላምታ ተመሳሳይ ነው፡፡ ሔዋንን ስላም ለኪ ብሎ ነው ያታለላት የይሁዳም ሰላምታ ሰይጣናዊ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን ወቅትና ሁኔታ ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ሰለምታ ልውውጥ የለም፡፡ ዛሬ እየተስተዋለ ያለው ይኽው ሰላምታ ያለመለዋወጥ ሁኔታ ስርወ መሰረቱ ይህ ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ እዚህ ትውልድ ላይ ደርሷል፡፡ ይቀጥላልም፡፡