Showing posts with label ግጥም. Show all posts
Showing posts with label ግጥም. Show all posts

Tuesday, May 26, 2015


                                      ተዋሕዶ-በደም


በደም ተመሥርተሽ
በደም ተገንብተሸ
በደም ተዋሕደሽ
በደም ተሰራጭተሸ

Tuesday, January 27, 2015

አበው ይናገሩ

እስኪ ቀስቅሷቸው አበው ይናገሩ
የምንኩስና ግብር ምን ነበር ምሥጢሩ
የክርስትና ሕይወት ምን ነበር ተግባሩ
መቃብሩን ክፈቱና አበው ይመስክሩ፡፡

እኔስ ሰው አማረኝ የሃይማኖት ጀግና
ወልድ ዋሕድ ብሎ በእምነቱ የፀና
ጀግና ሰው አማረኝ ጠላት አሳፋሪ
ንጽህት ድንግል ብሎ እምነቱን መስካሪ፡፡

ቅዱስ ጳውሎስ

እርሱ እናቴ እኔን ቅሪት እያማጠኝ፤
በልጅነት ሊገላገል በሐሳብ ያረገዘኝ፤
በማኅፀን ሰፋድሉ በትምህርቱ እኔን ስሎ፤
በመዶሻው እኔን ጠርቦ አስተካክሎ፤
እጄን ይዘህ አለማምደህ እንዲያ ስድህ፤
ቃለ ነገር ቃለ ምሥጢር እየጋትህ፤
ጠንካራውን ጥሬ ቃሉን አስቆርጥመህ፤
አንተ አብይ ባሕር የትምህርት ውቅያኖስ፤
ምርጥ ዕቃ ማዕዘን ዕብነ አድማስ፤
በእንቁላል ቅርፊት ቀድቼ የረካሁኝ ከአንደበትህ፤
ርዕሰ እውቀት አንተ አፈ ዝናም በትምህርትህ፡፡
አሕዛበ-ምድር ማንነቴን በጠብታህ ጎበኘሃት፤

መቼም አይጨክን አይተዋት

የሄሮድስ ሰይፍ ቀልቷቸው
በስቃይ አልፋ ነፍሳቸው
በግፍ ያለቁ ሕፃናቱ
በአዳራሾችሽ ሲደሰቱ
በአማረው አክናፍ በረው በረው
ያለማቋረጥ አመስግነው
የእኒያ መላእክት ጥዑም ዜማ
እንዴት ይማረክ ሲሰማ
በአላውያን የግፍ ስለት
ከምድር ያለፉ ሰማዕታት
አክሊሉን ደፍተው በራሳቸው
በአምላክ ታብሶ እንባቸው
ለዓለም ዓለም ሲያርፉ
ከጠላት ወጥመድ ሲተርፉ