Showing posts with label ብሂለ_አበው. Show all posts
Showing posts with label ብሂለ_አበው. Show all posts

Saturday, March 7, 2015

ርዕትዕት ሃይማኖቶሙ ለቅዱሳን አበዊነ


በሰው ቂም አትያዝ በሰው ላይ ያለውን ቂም በልቦናው የሚያሳድር ሰው ጸሎቱ
ቅድመ እግዚአብሔር አትደርስምና ከአርዮሳውያን ጋር አትጸልይ እሊህም መናፍቃን ናቸው፡፡ ከአህዛብም ጋር ቢሆን፡፡(መዝ 4÷4-36(37) ፣ ማቴ 5 ÷ 5-14 ፣ ሮሜ 4 ÷ 4-19-2)


አንተ ሰውነትህን ለማድከም በምትጾምባቸው ዕለታት ወንድምህ ሊጠይቅህ ቢመጣ
እግዚአብሔርን ደስ በምታሰኝ በበጎ ሕሊና በፍቅር ሆነህ ከእርሱ ጋር ተመገብ ይህንንም የምነግርህ  የጌታ ጾም በሆነበት ዕለታት ትበላ ዘንድ አይደለም፡፡ እሊህም ረቡዕ እና
አርብ  አርባውም (ዓብይ ጾም) ቀን ናቸው፡፡ አንተ ብቻ በራስህ ፈቃድ
በምትጾምበት ቀን ነው እንጂ ይኸውም  ሰኞ ማክሰኞ ሐሙስ ነው፡፡
(ዳን 10 ÷ 2-3፣ማቴ 6÷16-18)

በቅዳሜ ቀን ግን መጾም አይገባም ፡፡በቅዳሜ ቀን ፀሐይ እስኪጠልቅ  መጾም የሚገባ ስራ አይደለም፡፡ እሁድ ግን በጠዋት  እጅግ ማልደህ ወደ ቤተክርስቲያን ሂድ ስትሄድም ልቦናህን በማባከን ወዲያ