በሰው ቂም አትያዝ በሰው ላይ ያለውን ቂም በልቦናው የሚያሳድር ሰው ጸሎቱ
ቅድመ እግዚአብሔር አትደርስምና ከአርዮሳውያን ጋር አትጸልይ እሊህም መናፍቃን ናቸው፡፡ ከአህዛብም ጋር ቢሆን፡፡(መዝ 4÷4-36(37) ፣ ማቴ 5 ÷ 5-14 ፣ ሮሜ 4 ÷ 4-19-2)
አንተ ሰውነትህን ለማድከም በምትጾምባቸው ዕለታት ወንድምህ ሊጠይቅህ ቢመጣ
እግዚአብሔርን ደስ በምታሰኝ በበጎ ሕሊና በፍቅር ሆነህ ከእርሱ ጋር ተመገብ ይህንንም የምነግርህ የጌታ ጾም በሆነበት ዕለታት ትበላ ዘንድ አይደለም፡፡ እሊህም ረቡዕ እና
አርብ አርባውም (ዓብይ ጾም) ቀን ናቸው፡፡ አንተ ብቻ በራስህ ፈቃድ
በምትጾምበት ቀን ነው እንጂ ይኸውም ሰኞ ማክሰኞ ሐሙስ ነው፡፡
(ዳን 10 ÷ 2-3፣ማቴ 6÷16-18)
እግዚአብሔርን ደስ በምታሰኝ በበጎ ሕሊና በፍቅር ሆነህ ከእርሱ ጋር ተመገብ ይህንንም የምነግርህ የጌታ ጾም በሆነበት ዕለታት ትበላ ዘንድ አይደለም፡፡ እሊህም ረቡዕ እና
አርብ አርባውም (ዓብይ ጾም) ቀን ናቸው፡፡ አንተ ብቻ በራስህ ፈቃድ
በምትጾምበት ቀን ነው እንጂ ይኸውም ሰኞ ማክሰኞ ሐሙስ ነው፡፡
(ዳን 10 ÷ 2-3፣ማቴ 6÷16-18)
በቅዳሜ ቀን ግን መጾም አይገባም ፡፡በቅዳሜ ቀን ፀሐይ እስኪጠልቅ መጾም የሚገባ ስራ አይደለም፡፡ እሁድ ግን በጠዋት እጅግ ማልደህ ወደ ቤተክርስቲያን ሂድ ስትሄድም ልቦናህን በማባከን ወዲያ