Friday, December 16, 2016


              

     ሕልመ ሌሊት
 በጠለቀ
እንቅልፍ ላይ ሳሉ የሚከሠት ሕልመ ሌሊትን እንደ ኃጢአት እንዲቆጠርና እንዳይቆጠር የሚያደርጉ የተለያዩ ሁኔታዎች አሉ:: ስለዚህ ሕልመ ሌሊትን በጥቅሉ ኀጢአት ነው ወይም አይደለም ማለት አይቻልም:: ነገር ግን እንደ ኀጢአት እንዲቆጠር የሚያደርጉ ሁኔታዎችን በመጠኑ መዘርዘር ይቻላል::
/. አጋንንት የሰውን ልጅ በተኛበት ክፉ ክፉ ሕልም በማሳየት ይፈትኑታል:: አንድ ጊዜ የተራቆተ የሴት ገላ; በሌላ ጊዜ ደግሞ እንደ ወንድና ሴት አለሌና ባዝራ እየሆኑ ሲጨዋወቱና ሲደራረጉ በምትሐት ያሳዩታል:: በዚህ ጊዜ እርሱም በዝሙት ሐሳብ ይሳብና በሕልሙ ዝሙት ሲፈጽም ያድራል:: በዚህ መልኩ የተከሠተ ሕልመ ሌሊት "ጸዋግ" ወይም "ኅሡም" ሕልም ይባላል:: ክፉ
ወይም ጥፉ ሕልም ማለት ነው::
በዚህ መልኩ አጋንንት ሰውን እንደሚዋጉት
በመጽሐፈ መነኮሳት እንዲህ ተጽፏል:: "ይትቃተልዎ ሰይጣናት በመዓልት
በሕሊናት እኩያት ወበሌሊት በአሕላማት ኅሡማት" በአማርኛ "ሰይጣናት
የሰውን ልጅ ቀን ቀን ክፉ ሐሳብ በማሳሰብና በማሠራት በሌሊት ደግሞ ዝሙት የሞላበት አስጸያፊ ሕልም በማሳየት ይዋጉታል"
                               ብፁዕ አቡነ ዜና ማርቆስ



      አቡነ ዜና ማርቆስ አባታቸው ዮሐንስ እናታቸው ማርያም ዘመዳ /ዲቦራ/ ይባላሉ፡፡ አባታቸው ዮሐንስ የአቡነ ተክለ ሃይማኖት አባት የአቡነ ጸጋ ዘአብ ወንድም ናቸው፡፡ እናታቸው ደግሞ የአቡነ ቀውስጦስ እኅት ናቸው፡፡ አቡነ ዜና ማርቆስ በወንጌላዊው ቅዱስ ማርቆስ ብሥራት የተጸነሱ አባት ናቸው፡፡ እኚህ አባት በተወለዱ በሦስተኛው ቀን ከእናታቸው እቅፍ ወርደው እሰግድ ለአብ እሰግድ ለወልድ እሰግድ ለመንፈስ ቅዱስ ብለው ሦስት ጊዜ ሰግደዋል፡፡


የገና ዛፍ
የገና ዛፍ ከየት መጣ ከእፅዋት ሁሉ የጽድ ዛፍ ብቻስ
ለምን ሆነ ?
የጌታችንና የአምላካችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርሰረቶስ
የልደት በዓል ሲከበር ዘውትር እያየናቸው ካሉና የበዓሉ አንድ
አካል እየሆኑ ከመጡ ነገሮች መሀከል ዋነኛው የገና ዛፍ ነው።
ይህን የገና ዛፍ አብዛኞቻችን ዝም ብለን ከማድረግ ባለፈ መቼቱ
የት እንደሆነ ምን አይነት ምስጢር እንዳለው የምናውቅ
አይመስለኝም ነገር ግን የቤተክርስቲያን ታሪክ ወደኋላ መለስ
ብለን ስናይ ምንጩ ከወዴት እንደሆነ ይነግረናል የመጀመሪያዎቹ
ክርስቲያኖችና ሐዋርያት በነበሩበት ዘመን ራሳቸውን የእውቀት
ባለቤት አድርገው የሚቆጥሩ በክርስትና ላይ የመጀመሪያውን
የምንፍቅና ትምህርት ማንሳት የጀመሩ  ግኖስቲክስ የሚባሉ
ሃሳውያን ነበሩ የስማቸው ትርጉም በግሪክ ቋንቋ ጠቢባን
አዋቂወች ማለት ነው። መሪያቸው ስምኦን መሰሪ ይባላል ይህ
ሰው በመጽሀፍ ቅዱስ ውስጥ ሐዋርያትን የመንፈስ ቅዱስን ፀጋ
በገንዘብ እንዲሸጡለት ጠይቋቸው የነበረ ደፋር ሰው ነው።
ታዲያ እነዚህ እርሱ የሚመራቸው እራሳቸውን ጥበበኞች ብለው
የሚጠሩ መናፍቃን ከፍልስፍና ሃይማኖታቸው ብዙ
አስተምህሮዎች መካከል ዋነኛው ሁለት አምላኮች አሉ
ብለው የሚያምኑት ነገር ሲሆን እነዚህ አማልክት አንዱ ክፉ
አንደኛው ደግሞ ደግ ናቸው ይላሉ።መልካም የሆኑና ጥሩ ናቸው

Saturday, December 10, 2016


                        ጾመ ነቢያት

 

እንኳን ለፆመ ነቢያት በሰላም ና በጤና አደረሳችሁ!፡፡ ፆሙ የሰላም የፍቅርና የደስታ ይሁንልን፡፡ ለብርሃነ ልደቱም በሰላም ያድርሰን!፡፡

          

     ዘመኑ ጾመ ነቢያት የተባለበት ምክንያት ነቢያት የተናገሩት ትንቢት ስለ ተፈጸመበት እንዲሁም በየዘመናቱ የተነሡ ነቢያት እግዚአብሔር ወደፊት ሊያደርግ ያሰበውን በእምነት ዓይን እያዩ ምሥጢር ተገልጦላቸው የራቀው ቀርቦ የረቀቀው ገዝፎ እየተመለከቱ ያዩትም መልካም ነገር እንዲደርስላቸው ስለ ጾሙ ስለ ጸለዩ ነው፡፡ ነቢያት ስለ ኢየሱስ ክርስቶስ መወለድ፣ ወደ ግብፅ ስለ መሰደድ፣ በባሕረ ዮርዳኖስ ስለመጠመቅ፣ በትምህርተ ወንጌል ጨለማውን ዓለም ስለ ማብራቱ፣ ለሰው ልጆች ድኅነት ጸዋትወ መከራ ስለመቀበሉና ስለ መሰቀሉ፣ ስለ ትንሣኤው፣ ስለ ዕርገቱና ስለ ዳግም ምጽአቱ ትንቢት ተናግረው አላቆሙም፤ ለአዳም የተሰጠው ተስፋ ተገልጦላቸው ለተናገሩት ትንቢት ፍፃሜ እንዲያደርሳቸው ፈጣሪያቸውን ተማፀኑትም እንጂ፡፡ በየዘመናቸው «አንሥእ ኃይለከ፣ ፈኑ እዴከ፤ ኃይልህን አንሳ እጅህንም ላክ» እያሉ ጮኹ፡፡ በጾምና በጸሎት ተወስነውም ሰው የሚሆንበትን ጊዜ በቀናት፣ በሳምንታት፣ በወራትና በዓመታት ቆጠሩ፡፡ ለምሳሌ ነቢዩ ኤርምያስ ስለ ሥጋዌው ትንቢት በተናገረ በ446 ዓመት ጌታችን ከእመቤታችን ከሥጋዋ ሥጋ ከነፍሷ ነፍስ ነስቶ ሰው ሆኗል፡፡
ነቢያት ተስፋው በዘመናቸው ተፈጽሞ በዓይነ ሥጋ ለማየት ባይችሉም እግዚአብሔር «የማያደርገውን አይናገር የተናገረውን አያስቀር» ብለው አምነው ከወዲሁ ተደሰቱ፡፡ ለዘመነ ሥጋዌ ቅርብ የነበሩት እነ ኢሳይያስ ጾሙ እንዴት መፈጸም እንዳለበት ተናግረዋልም፡፡ ኢሳ 58-1፡፡ በመሆኑም በጌታ ልደት ትንቢተ ነቢያት ስለ ተፈጸመበት ይህ ጾም «የነቢያት ጾም» ይባላል፡፡ የወልደ እግዚአብሔርን ሰው መሆን ያስተማሩበት የሰው ልጆች ተስፋ የተመሰከረበት የምሥራቹ የተነገረበት ስለሆነም «ጾመ ስብከት» ይባላል፡፡

Friday, September 23, 2016

                                ደመራ                  


        ደመራ፣ ደመረ ጨመረ ካለው የግእዝ ቃል የመጣ ነው ትርጉሙ መጨመር (መከመር) ማለት ነው፡፡ኦሪታውያን ከመስከረም ፲፭-፳፪ ለስምንት ዕለታት በዓለ መጸለትን ያከብሩ ነበር፡፡(ዘሌ.፳፫፥፮) በዓሉን የሚያከብሩት በብዙ መንገድ ሲሆን፤ እንጨት እየሰበሰቡና እየከመሩ ማታ ማታ በእሳት እያቃጠሉ በመጫወት ያከብሩታል፡፡ ኋላ ግን ተሸሽሎ የእሳት ማንደጃ ቀን በመስከረም ፲፯ ላይ ቆሞአል፡፡
ያም በዓል ከዘመነ ሐዲስ ሲደርስ የመስቀል ደመራ ተብሎ ተሰይሟል፡፡ የኢትዮጵያ ሕዝብ በታላቅ ናፍቆትና አክብሮት ከሚያከብራቸው በዓላት አንዱ መስከረም ፲፮ ዕለት (በዋዜማው) የሚከበረዉ የደመራ በዓል ሲሆን በማግስቱ በመላ ኢትዮጵያ ብሔራዊ በዓል ሆኖ ጥንትም ሆነ ዛሬ በታላቅ ድምቀት የሚከበረው የመስቀል በዓል ነው፡፡  

               የመስቀል በዓል ማክበር መቼ ተጀመረ?
የመስቀል ክብረ በዓል ከክርስትና እምነት ጋር ተያይዞ የመጣ ነው፡፡ የታላቁ ቆስጠንጢኖስ እናት ንግሥት ዕሌኒ ከቁስጥንጥያ ተነሥታ ድሆች ክርስቲያኖችን ለመርዳትና አብያተ ክርስቲያናትን ለመሥራት በ፫፻፳፮ ዓ.ም ወደ ኢየሩሳሌም ሄደች፡፡
ኢየሩሳሌም በደረሰች ጊዜ የጌታች መስቀል ተአምራት እንዳያደርግ አይሁዶች በምቀኝነት ቀብረውት ነበርና የተቀበረበትን ቦታ የሚያሳያት አጥታ  በመፈለግ ብዙ ጊዜ አሳለፈች በኋላ ግን አንድ ኪራኮስ የሚባል እስራኤላዊ አካባቢውን ነግሯት ደመራ አስደምራ ዕጣን አጢሳ ወደ ፈጣሪዋ ብትማጸን የዕጣኑ ጢስ ወደ ሰማይ ከወጣ በኋላ ተመለወሶ መስቀሉ የተቀበረበትን ስፍራ አመለከተ፡፡ እርሷም በምልክቱ መሰረት ብታስቆፍር የጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ክቡር መስቀል አገኘች፡፡ የእርሱ መስቀል ለመሆኑ ድውያንን በመፈወሱ፣ አንካሳ በማበራቱ፣ ጎባጣ በማቅናቱ ታውቋል፡፡ ይኽንንም ይዞ ኢትዮጵያዊው ሊቅ ቅዱስ ያሬድ ሰገደ ጢስ ብሎ በድጓው ጽፎት ይገኛል፡፡ ስለዚህ በየዓመቱ የመስቀልን በዓል ስናከብር ደመራ የምንደምረውና የምናበራው ንግሥት ዕሌኒ አብነት በማድረግ ነው፡፡
በተጨማሪም ንግሥት ዕሌኒ መስቀሉን ባገኘች ጊዜ የደስታዋን መልእክት ለልጇ እንዲደርሰው ለማድረግ እንዳሁኑ ዘመን ስልክና ሬድዮ ስላልነበር በዚያን ጊዜ መልእክትን ሩቅ ሥፍራ ለማስተላለፍ ሲፈልጉ በየተራራው ቃፊሮችን (መልእክተኞችን) መድበው መልእክቱን ከሚተላፍበት አቅራቢያ ተራራ ላይ ያለው ቃፊር (መልእክተኛ) ችቦ በማብራት ከርሱ በኋላ ተራራ ላይ ላለው ቃፊር ምልክትን በማሳየት መልእክቱን ያስተላልፋ፤ ሌላኛውም ቃፊር ችቦን እያበራ ሌላኛው ምልክት በማሳየት መልእክቱ መድረስ የሚገባው ቦታ በዚህ መልኩ ያስተላልፋ ነበር፡፡ ንግሥት ዕሌኒም ይህንን ዘዴ በመጠቀም የመስቀሉ መገኘት ወሬ (የምሥራች ዜና) ቁስጥንጥንያ እንዲደርስ አደረገች ልጇ ቆስጠንጢኖስም መልእክቱ እንደደረሰው ወደ ኢየሪሳሌም ሂዶ እናቱን አግኝቶ ብዙ ስጦታ አበርክቶላታል እርስዋም የቤተክርስቲያኑም መሠረት ወዲያው እንዲጣል አደረገች የደመራ ማብራት ሥርዓት ከዚህ ሲያያዝ የመጣ ነው፡፡ የበረከት በዓል ያድርግልን፡፡

Saturday, September 10, 2016

                        ዕንቁጣጣሽ

    ዕንቁጣጣሽ በኢትዮጵያውያን ዘንድ የደስታ፣የብሩህ ተስፋና የአዲስነት ስሜት የሚያሳድር ነው፡፡ዕንቁጣጣሽየሚለው ስያሜ በቃል የተነገረ እንጂ በጽሑፍ የሠፈረ አልተገኘም፡፡ ኖም በቃል ትውፊት ሲነገር እንደ መጣ ...

      *ዕንቁ ብሎ አዕናቁ ከግእዝ የተወረሰ ቃል ነው፡፡ ዕንቁ ለአንድ፤ አዕናቁ ለብዙ ይነገራል፡፡ ጣጣሽ፡- “ፃዕ ፃዕከሚለው የግእዙ ቃል የተወረሰ ነው በአማርኛ ጣጣ፣ መባዕ፣ ግብር፣ መፍቀድ፣ ገጸ በረከት /በረከተ ገጽ/ ማለት ይሆናል፡፡ መጽሓፍተ ብሉያት ወደ እግዚአብሔር የሚቀርበውን መባዕ፣ የሚገባውን ግብርፃዕፃዕይሉታል፡፡ በየዓመቱ ዕንቁጣጣሽ ማለታችን ‹‹ የዕንቁጣጣሽ ግብር፣ የእንቀጣጣሽ ገጸ በረከት ነው ›› ብለን የምሥራች ማሰማታችን ነው፡፡
በሃገራችን ለመጀመሪያ ጊዜ ዕንቁጣጣሽ የተበረከተው ለቀዳማዊ ምንይልክ /ምኒልክ/ እናት ለንግሥት ማክዳ ነው፡፡ ንግሥት ማክዳ ቀዳማዊ ምንይልክን /ምኒልክን/ በወለደች ጊዜ ሕዝቡ ንጉሥ ተወለደ ብሎ እልል እያለ ገጸ በረከት አቅርበዋልየአበባ ዕንቁጣጣሽ መባሉም መጀመሪያ ለንግሥቲቱ ስለ ተገበረ ነው፡፡ ለንጉሥ ቢሆን ኖሮ ‹‹ዕንቁ ፃዕፃሁ›› ይባል ነበር እንጂ ‹‹ዕንቁጣጣሽ›› አይባልም ነበር፡፡ በሸዋም ሕዝቡ ግብር አለብኝ ሲል ‹‹ጣጣ አለብኝ ›› ይላል፡፡

Friday, August 19, 2016

አስተርእዮተ እግዚአብሔር በደብረ ታቦር


‹‹አስተርእዮ›› ሥርወ ቃሉ ‹‹አስተርአየ (አርአየ) = አሳየ፣ ገለጠ፣ ታየ፣ ተገለጠ›› የሚለው የግእዝ ግስ ሲኾን ትርጕሙም ‹‹መታየት፣ መገለጥ፣ ማሳየት፣ መግለጥ›› ማለት ነው /ኪዳነ ወልድ ክፍሌ/፡፡ ‹‹አስተርእዮተ እግዚአብሔር በደብረ ታቦር›› የሚለው ሐረግም ‹‹የእግዚአብሔር በታቦር ተራራ መገለጥ›› ወይም መታየት የሚል ትርጕም ያለው ሲኾን ይህም ከእግዚአብሔር አንድነትና ሦስትነት ጋር የተያያዘ እንደዚሁም ከምሥጢረ ሥጋዌና ከነገረ ድኅነት ጋር የተሳሰረ ታላቅ ምሥጢርን የያዘ መገለጥ ነው፡፡
ከዚህ ላይ ‹‹አስተርእዮተ እግዚአብሔር›› ስንል የአብ፣ የወልድ፣ የመንፈስ ቅዱስ መገለጥ ማለታችን መኾኑን ለማስታዎስ እንወዳለን፡፡ ‹‹እግዚአብሔር›› የሚለው ቃል ሦስቱም አካላት (ቅድስት ሥላሴ) በጋራ የሚጠሩበት መለኮታዊ ስያሜ ነውና፡፡ ‹‹አንሰ ሶበ እቤ እግዚአብሔር እብል በእንተ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ ከመ በአሐዱ ስም ሥሉሰ ያምልኩ፤ እኔ ‹እግዚአብሔር› በአልሁ ጊዜ ስለ አብም፣ ስለ ወልድም፣ ስለ መንፈስ ቅዱስም እናገራለሁ፤ (ምእመናን) በአንዱ ስም (በእግዚአብሔር) ሦስቱ አካላትን ያመልኩ ዘንድ›› እንዳለ ቅዱስ ጎርጎርዮስ ነባቤ መለኮት /ሃይማኖተ አበው/፡፡
ቅዱሳት መጻሕፍት እንደሚነግሩን እግዚአብሔር አምላክ በብሉይም ኾነ በሐዲስ ኪዳን በአንድነቱ በሦስትነቱ በግብር (በሥራ)፣ በራእይና በገቢረ ተአምራት በልዩ ልዩ መንገድ ለፍጡራኑ ተገልጧል፡፡ በብሉይ ኪዳን ልዩ ልዩ ምልክት በማሳየት፤ በቅዱሳን ነቢያትና በመሣፍንት፣ በነገሥታት፣ በካህናትና በነቢያት ላይ በማደር ወይም በራእይ በማነጋገር፤ በተጨማሪም በጻድቃኑ ላይ ቸርነቱን በማሳየት፣ በክፉ አድራጊዎች ላይ ደግሞ መቅሠፍቱን በመላክ ሲያደርጋቸው በነበሩ ተአምራቱና ሥራዎቹ ይገለጥ ነበር፡፡