Showing posts with label መንፈሳዊ_ወግ. Show all posts
Showing posts with label መንፈሳዊ_ወግ. Show all posts

Monday, March 30, 2015

ከሞት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ /ክፍል ፩/



እንደምን ሰነበታችሁ ውድ ክርስቲያኖች? . . . እስቲ አንዲት ጥያቄ ልጠይቃችሁ?
ሞትን ታውቁታላችሁ?
እኔማ አሁን ባለፈው ዕለት እንዳጋጣሚ አገኘሁት እና እባክህ ቃለ መጠይቅ ላድርግህ ብዬ ብጠይቀው አሻፈረኝ አለ፡፡ ብለው ብሰራው . . . ወይ ፍንክች!!! "ኧረ ባክህ እንደው ለአጭር ሰዓት ላስቸግርህ?" እሱ መቼ ሰምቶኝ፡፡
በመጨረሻም "በዮሐንስ አፈወርቅ?" ብዬ ስለምነው "ያኔ አስራ ሁለት አመት ገትሮ አቁሞኛል፡፡ አሁን ደግሞ ሃያ አራት ዓመት ያደርግብኝ እንደሆነ መከራ ታሳየኛለህ፡፡" አለና እሺ አለኝ፡፡ እኔም የነገረኝን በማስታወሻዬ ፃፍኩት፡፡ ይኸው አሁን በክፍል በክፍል እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌ ለእናንተ እንደሚከተለው አቀረብኩት . . .

ጥያቄ፡-   ስለትውልድህ እና እድገትህ ብታጫውተኝ?

Friday, March 6, 2015

ልብ ብለው ያንብቡት!

             
ከእለታት ባንድቀን አባት የሚጠባ ልጁን እንዲጠብቅለት ከውሻው ጋር ትቶት ወደ አደን ይሄዳ።  ከአደን ሲመለስ ውሻውን በደም ተጨማልቆ በሩ ላይ አገኘው። ውሻው የተጨማለቀበትን ደም ሲመለከት ልጁን በልቶት እንደሆነ ገመተ። ልክ ሁላችንም እንደምንገምተው በጣም ተናዶ ለአደን ይዞት የነበረውን መሳሪያ አቀባበለና ውሻውን የጥይት ሩምታ አወረደበት።የተረፉ የልጁን አካል ለማየት ወደ ውስጥ እየሮጠ ገባ። ነገር ግን ልጁ አንዳችም መጥፎ ነገርአላገኘውም። ይልቁንስ ከፊትለፊት በደም የተጨማለቀ ተኩላ ሞቶ ተመለከተ።ተመልከቱ ስሜቱ ሸፍኖት የዕድሜ ልክ ፀፀት የሆነበት ስራ ፈፀመ!!!። ስንቶቻችን ነገሮችን ሳናረጋግጥ ከብዙዎች
ተቆራርጠናል?  ልልህ የፈለኩት አንተ የሰው ልጅ ሆይ! ፊትለፊት በምታይበት አይንህ ብቻ አትፍረድ! አዕምሮህንም ለፍርዱ ሹመት ስጠው! በችኮላ ስህተትን ሰርተህ ህይወትህን በሙሉ የሚፀፅትህ ነገር ውስጥ እንዳትገባ ተጠንቀቅ!!!።