Monday, February 15, 2016

ተረፈ ካም

ካም ከሦስቱ የኖህ ልጆች ሁለተኛው ነው፡፡ ሴም ታላቅ ወንድሙ ያፌት ደግሞ ታናሹ፡፡ የጥፋት ውሃ ጎድሎ ምድርም ፈጽማ ከደረቀች በኋላ “አኀዘ ኖህ ይትገበራ ለምድር”  ኖህ ምድርን ይኮተኩታት ይቆፍራት ያርማት ጀመር፡፡ የወይን ሐረግም ተከለ፡፡ ከዚያው ከተከለው ወይን ጠጥቶ ሰከረ፡፡ በድንኳኑ ውስጥም ታራቆተ ፡፡


" ወርእዮ ካም አቡሁ ለከነዓን ዕርቃነ አቡሆሙ ሰሐቀ ወወፅአ ወነገሮሙ ለክልኤሆሙ አኃዊሁ በአፍአ" (የከነዓን አባት) ካምም የአባታቸውን ዕርቃን አይቶ ሳቀ፤ ተሳለቀ፡፡ ወደ ውጭ ወጥቶም ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው፡፡ 

"ወነሥኡ ሴም ወያፌት ልብሰ ወወደዩ ላዕለ ዘባናቲሆሙ ወሖሩ ድኅሪተ ወከደኑ ዕርቃነ አቡሆሙ" ያፌትና ሴም ልብስ ወስደው ሁለቱም በትከሻቸው ላይ አደረጉ፡፡ የኋሊት ሄደው የአባታቸውን ዕርቃን ሸፈኑ፡፡ በዓይኖቻቸው የአባታቸውን እራቁትነት ለማየት እንኳን አልደፈሩም፡፡

"ወገፆሙ ድኅሬሆሙ አግብኡ ወኢርእዩ ዕርቃነ አቡሆሙ" ይላል፡፡ ፊታቸውን ወደ ኋላ አዙረው ወጡ፡፡ የአባታቸውን እርቃን አላዩም፡፡

ከዚህ በኋላ የወይን ስካር ፈጽሞ አእምሮ አይነሳምና ኖህ ከስካሩ ነቃ  ታናሹ ልጁ ካም እንደዘበተበት፤ ያፌትና ሴም ልባሳቸውን እንዳለበሱት ባወቀ ጊዜ በታናሹ ልጁ ካም አዘነበት፤