Saturday, February 28, 2015

3ተኛ ሳምንት ምኵራብ



ምኩራብ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ነው፡፡ ምኵራብ ማለትም ሰቀላ መሰል አዳራሽ ማለት ነው። አይሁድ ስግደትና መሥዋዕታቸውን የሚያቀርቡት በኢየሩሳሌም ባለው መቅደስ ብቻ ነው ብለው ቢያምኑም (ዮሐ 420) ፤በየተበተኑበት ቦታ ምኩራብ እየሠሩ ትምህርተ ኦሪትን በመማር ሃይማኖታቸውን ያፀኑ ነበር። ከአስር በላይ አይሁዳውያን በአንድ መንደር  ካሉ  አንድ ምኵራብ  እንዲሰራላቸው የአይሁድ ህግ ያዛልአይሁድ በምኲራቦቻቸው የሕግንና የነቢያትን መጻሕፍት /የብራና ጥቅሎች/ በአንድ ሣጥን ውስጥ ያስቀምጣሉ፡፡ በመሆኑ የጸሎት ሥፍራዎቻቸውን ለትምህርትና ለአምልኮ ይጠቀሙባቸዋል፡በምኩራብ አይሁድ ይጸልያሉ፣ ይማራሉ፣ ያስተምራሉ በአጠቃላይ ስርዓተ አምልኮን ይፈጽማሉ፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ምራብ ለማስተማር በገባ ጊዜ ግን በተቃራኒው መሸጫ እና መለወጫ ሆነው ርግብንና በሬን ሲነግዱ እንደነበረ ተጽፏል፡፡ጌታችንም ይህንን አይቶ እንደፈለጋችሁ ሁኑ ብሎ ዝም አላላቸውም፡፡

Friday, February 27, 2015

አባ ሳሙኤል ዘደብረ ሃሌ ሉያ



አባ ሳሙኤል የታላቁ ርዕሰ መነኮሳት የአባ እንጦንስ ተከታይ የደብረ ሃሌ ሉያ ገዳም መሥራች፣ በ፲፬ኛው ምዕተ ዓመት ይኖሩ የነበሩ፣ ሀብተ ትንቢት የተሰጣቸው ታላቅ አባት ናቸው፡፡ አባ ሳሙኤል የመሰረቱት ገዳም ደብረ ሃሌ ሉያ፤ በክብሩ ከደብረ ሲናና ከደብረ ዘይት የማያንስ መሆኑ ይነገርለታል፡፡ ስለ አባ ሳሙኤል ገድላቸው እንዲህ ይተርክላቸዋል፡፡
ስሟ መርታ በተባለች ሀገር የሚኖሩ፣ ሕገ እግዚአብሔርን እንደ ኖኅ እንደ አብርሃም የጠበቁ፣ በትውልድም የቡሩካን የደጋግ ሰዎች ወገን የሆኑ ስማቸው ይስሐቅ ለነ እግዚእ የሚባሉ ሰው ነበሩ፡፡ እኒህም ሰው ቅድስትነ ማርያም የምትባል ሴት በሕግ አገቡ፤ እርሷም እንደ ሃና እንደ ኤልሳቤጥ እግዚአብሔርን የምትፈራ፣ ለድሃ የምትራራና በሁሉ ዘንድ የተወደደች ነበረች፡፡ በትውልድም የክቡራን ወገን ነበረች፤ ሙት የሚያስነሱ ድውያን የሚፈውሱ አቡነ ዓቢየ እግዚእ የተባሉ ጻድቅ ወንድም ነበሯት፡፡ ልጅ እንደፀነሰችም ባወቀች ጊዜ፤ ቡራኬ ለመቀበል ወደ እርሳቸው ለመሄድ መንገድ ጀመረች፡፡ እዚያም በደረሰች ጊዜ አቡነ ዓቢየ እግዚእ ከደቀ መዛሙርቶቻቸው ጋር ሳሉ፣ እህታቸው ስትመጣ ስላዩአት፤ አጠገባቸው ከመድረሷ አስቀድሞ ግንባራቸውን መሬት አስነክተው ሰገዱላት፡፡ ደቀ መዛሙርቱም ይህን በማየታቸው በመደነቅ "አባታችን ለዚህች ሴት በምን ምክነያት ሰገዱላት?" በማለት ጠየቋቸው፡፡ እርሳቸውም "ልጆቼ ሆይ ለእርሷ የሰገድኩ አይምሰላችሁ፤ እኔ የሰገድኩት በብርሃኑ ምድረ ኢትዮጲያን ለሚያበራት፣ ዕንቁ ባሕርይ ለሆነ በማኅፀንዋ ላለው ልጅ ነው፡፡ እሱም በጸሎቱ የሚጠብቅ፣ በትሩፋቱ የሚያፀድቅ፣ በትምህርቱ ስፍር ቁጥር የሌላቸውን ሕዝብ የሚያድን፣ የኔንም ስም የሚያስጠራ ነው" የሚል ቃለ ትንቢት መለሱላቸው፡፡

መባከን በመንፈሳዊ አገልግሎት


መንፈሳዊ አገልግሎት ሲባል ሁሌም የምትታወሰው ቤተ-ክርስቲያን ናት፡፡ይህ አገልግሎት የቤተ ክርስቲያንን ህይወት በእጅጉ የተንተራሰ  ሠፊ የቅድስና መንገድ ነው፡፡ከዚህ ህይወት የምንረዳው አንዱና ትልቁ ነገር የቤተ ክርስቲያን ህይወት የተጋድሎ ህይወት መሆኑን ነው፡፡ይህ ትግልም ለግል ክብርና ዝና ወይም እንደ ህልም ታይቶ ለሚጠፋው ለዚህ ዓለም ሥልጣን እና ምቾት ሳይሆን በስጋ የተገለጠው እግዚአብሔር ወልድ የገለጠውን የመዳን ምስጢርና እውነት ለመመስከርና ይህን የእውነት ቃል ለሰዎች ለማዳረስ የሚደረግ ተጋድሎ ነው፡፡

እንግዲህ በዚህ ህይወት ውስጥ ብዙ ተቃራኒዎች አሉ፡፡ ነገር ግን ዛሬ ማንሳት የፈለግነው ስለተቃራኒ ፈተናዎች ሳይሆን መንፈሳዊ አገልግሎት ራሱ የዲያብሎስ የቅንብር ስራ ሊሆን እንደሚችል እና ብዙዎቻችን በዚህ መንፈሳዊ መሰል አገልግሎት ተጉዘን ፍጻሜያችን ግን ምን ሊሆን እንደሚችል እንመለከታለን፡፡ዲያብሎስ የሰውን ልጆች ከጽድቅ መንገድ ማራቅ የተለመደ ስራው ነው፡፡ የሰው ልጆች ዕለት ዕለት ወደ አምልካቸው ወደ እግዚአብሔር በሚያደርጉት የቅድስና ጉዞ እንቅፋት በመሆንም ሊያገኙት ከነበረው ክብር እና ጸጋ ፈጽሞ እንዲለዩ ያደርጋል፡፡እንግዲህ ይህንን ተግባሩን በተለያዩ መንገዶች እና ስልታዊ በሆኑ ዕቅዶች ያከናውናቸዋል፡፡ ከእነዚህም ውስጥ ተስፋ በማስቆረጥ፣ጥርጣሬ በመትከል፣በማዘግየት፣መልካም ምግባራትን

Wednesday, February 25, 2015

‹‹ከሃይማኖት ልዩነት ጋር ወደ ትዳር እያመራን ነው፡፡››

ከእጮኛዬ ጋር ከተዋወቅን ሁለተኛ ዓመት ሆኖናል፡፡ነገር ግን በሃይማኖት ከእኔ የተለየ በመሆኑና የፕሮቴስታንት እምነትን ስለሚከተል መግባባት አልቻልንም፡፡በዚህ ሁኔታ ትዳር መመሥረት በራሱ ከባድ ሆኖብኛል፡፡ምክርዎን እጠብቃለሁ፡፡

                                                                                                          ሜሮን ከአዲስ አበባ
እኅታችን በመጀመሪያ ለጥያቄሽ መፍትሔ ለማግኘት በመጻፍሽ አመሰግናለሁ፡፡ወደ ጥያቄው መልስ ስንሔድ ከላይ እንዳነሣሽው ጓደኛሽ የፕሮቴስትንት እምነት ተከታይ በመሆኑ መግባባት አቅቷችኋል፡፡ከዚህ ልዩነት ጋር ትዳር መመሥረቱ ደግሞ በራሱ ለልቦናሽ ከባድ ሆኖ ታይቶሻል፡፡በጥያቄሽ ያላነሣሽው እጮኛሽን ለመመለስ ያደረግሽውን ጥረት ነው፡፡ከዚህ ቀደም እርሱን አስተምሮ ወደ ትክክለኛው መንገድ ለመመለስ ጥረት አላደረግሽ ከሆነ ይህንን አስቢበት፡፡መምህራን አግኝተው እንዲያስተምሩት እውነቱን እንዲነግሩት አድርጊ፡፡መመለስ ከፈቀደም በስሜት እንይሆን የተወሰነ ጊዜ ሰጥተሽ ተመልከቺው፡፡

Tuesday, February 24, 2015

መንፈሳዊት ፍቅር


   ልዑል እግዚአብሔር ዓለምን ከፈጠረበት ጥበቡ ይልቅ ከልዕልና ወደ ትህትና ወደዚህች ምድር መጥቶ የሰዎች ልጆችን ያዳነበት ምስጢር እጅግ ረቂቅ ጥልቅ ነው፡፡ አምላካችን ለኛ ያለውን ፍቅሩን የገለጠው ክብሩን በውርደት ለውጦ ነው፤ጠላቶቹ ስንሆን ነው የወደደን፡፡እንግዲህ በጥልቅ መንፈሳዊ ስሜት በእውነት ካስተዋልን አምላክ ሰው የመሆኑ ምስጢርና ለቤዛነት የመጣበትን ዓላማ በቃልና በድርጊት የፈፀማቸውን ስራዎች ስናስብ ልባችን በቅንነትና በማስተዋል የተመላ ከሆነ ዘወትር ይህንን ቃላት ሊገልጹት የማይችሉትን ለኛ ያለውን ወደር የማይገኝለትን ፍቅሩን ለማድነቅ እንገደዳለን፡፡
 
 “ፍቅር ሰሐቦ ለወልድ ኃያል እመንበሩ ወአብፅሖ እስከለሞት” ፍቅር ኃያል ወልድን ከዙፋኑ
አወረደው እስከ ሞትም አደረሰው ተብሎ እንደተፃፈ፡፡የሰዎች ልጆችን ከባርነት ወደ ነፃነት፣ከመከራ ወደ ደስታ፣ ከሲኦል ወደ ገነት፣ ለመግባት ያስቻላቸው የመድሐኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ወደር የማይገኝለት ታላቅ ፍቅሩ ነው፡፡ስደት እና መንገላታት ውረደት እና በጥፊ መመታት፤መናቅ በብረት መቸንከር እነ በጦር መወጋት ለሰባኪው እና ለሰሚዎች፣ለፀሀፊው እና ለአንባቢዎች ቀላል መስሎ ቢታየንም አምላካችን ስለኛ ብዙ መከራ ተቀብሎ ህይወትን ሰጥቶናል፡፡ከፍ ያለው ፍቅሩ በክብደት መለኪያዎች ተመዝኖ ይህን ያህላል አይባልም፡፡ወርድ እና ቁመቱም ግምቱም አይታወቅም፡፡