Monday, March 30, 2015

ከሞት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ /ክፍል ፩/



እንደምን ሰነበታችሁ ውድ ክርስቲያኖች? . . . እስቲ አንዲት ጥያቄ ልጠይቃችሁ?
ሞትን ታውቁታላችሁ?
እኔማ አሁን ባለፈው ዕለት እንዳጋጣሚ አገኘሁት እና እባክህ ቃለ መጠይቅ ላድርግህ ብዬ ብጠይቀው አሻፈረኝ አለ፡፡ ብለው ብሰራው . . . ወይ ፍንክች!!! "ኧረ ባክህ እንደው ለአጭር ሰዓት ላስቸግርህ?" እሱ መቼ ሰምቶኝ፡፡
በመጨረሻም "በዮሐንስ አፈወርቅ?" ብዬ ስለምነው "ያኔ አስራ ሁለት አመት ገትሮ አቁሞኛል፡፡ አሁን ደግሞ ሃያ አራት ዓመት ያደርግብኝ እንደሆነ መከራ ታሳየኛለህ፡፡" አለና እሺ አለኝ፡፡ እኔም የነገረኝን በማስታወሻዬ ፃፍኩት፡፡ ይኸው አሁን በክፍል በክፍል እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌ ለእናንተ እንደሚከተለው አቀረብኩት . . .

ጥያቄ፡-   ስለትውልድህ እና እድገትህ ብታጫውተኝ?

Saturday, March 28, 2015

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ




ኒቆዲሞስ ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ የአይሁድ አለቃ እና መምህር ነበረ “ወሀሎ አሐዱ ብእሲ እምፈሪሳውያን ዘስሙ ኒቆዲሞስ መልአኮሙ ለአይሁድ” ዮሐ3÷1 እንዲል፡፡ ሳምንቱ (ሰንበቱ) በእርሱ የተሰየመበት ዋናው ምክንያት ይህ ሰው በሌሊት እየመጣ ምስጢረ ጥምቀትን፣ ዳግም ልደትን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ እግር ስር ቁጭ ብሎ የተማረበት ቀን መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም ትምህርቱ ጌታችን ዋና የሆነውን እና ሰው ከውሀ እና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግስት እንደማይገባ በግልጽ አስተምሮታል፡


ኒቆዲሞስ ከቀን ይልቅ በሌሊት መማርን ስለምን መረጠ? 


ኒቆዲሞስ ይህንን ያደረገው ስለሶስት ነገር እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይናገራሉ ያስተምራሉ፡፡

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ

ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ በዚህ እለት የፈሪሳውያን አለቃ ኒቆዲሞስ በሌሊት ወደ ጌታ መጥቶ ሲማር ጌታም ምስጢረ ጥምቀትን ዳግም ልደትን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው እየጠቀሰ ቅዱስ ያሬድ ዮሐ 3 ላይ ያለውን ወንጌል ስለዘመረው የእለቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ተብሏል፡፡


በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን ፡-                 ሮሜ 7፥ 1-19   
በንፍቅ ዲያቆን፡-                       1ዮሐ 4፥18-ፍጻሜ
በንፍቅ ቄስ ፡-                          የሐዋ 5፥ 34
ምስባክ፡-        


ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ፤
አመከርከነ ወኢተረክበ ዐመጻ በላዕሌየ፤
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፡፡

አማርኛ ፡-                


ልቤን ፈተንከው በሌሊትም ጎበኘኸኝ፤
ፈተንከኝ ምንም አላገኘህብኝም፤
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው፡፡


ወንጌል:-           ዮሐ 3 ፥1-20
ቅዳሴ:-            ቅዳሴ ማርያም

Wednesday, March 25, 2015

አብርሃ ወአጽብሐ

ቅዱሳን ነገስታት አብርሃ ወአጽብሐ አባታቸው ታዜር እናታቸው ሶፍያ/አህየዋ/ በቅድስና የሚኖሩ እግዚአብሔርን በቅድስና በንጽህና የሚያገለግሉ ነገር ግን ልጅ ያላገኙ መካኖች ነበሩ። ስለሆነም ጌታ ሆይ ደስ የሚያሰኝህ በትዕዛዝህም የሚኖር ልጅ ስጠን እያሉ እግዚአብሔርን ይለምኑ ነበር፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ስለ እግዚአብሔር ቸርነት ሲነጋገሩ ንግስት ሶፍያ የሐና እመ ሳሙኤልን ጸሎት በመጥቀስ እሷም እንደ ሐና ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን እንድትለምን ንጉሱን ጠየቀችው፡ ንጉሱም “ ኦ ብእሲቶ ሰናየ ኁለይኪ” አንቺ ሆይ መልካም አስበሻል በማለት በምክሯ ተስማምቶ ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን በጸሎት እንድትጠይቅ ፈቀደላት፡፡ ንግስት ሶፍያም የካቲት 18 ቀን ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን መለመን ጀመረች፡፡ ከጸሎቷም ጥቂቱ “ በኪሩቤል ላይ የምትኖር፣ የቀለያትንም (ጥልቅ ባህርንም) የምትመለከት ጌታዬ ፈጠሪዬ ሆይ አቤቱ ጸሎቴንና ልመንያን ስማኝ፣ ልቅሶየንም አድምጥ ቸላ አትበለኝ” የሚል ነበር፡፡

ደጓ ንግስት ሶፍያ በብዙ ጸሎትና እንባ ሱባኤዋን ለመጨረስ ስትቃረብ፣ አንድ ራእይ ተገለጠላት፣ እሱም ከተራራ ላይ የተተከለች ረዥም ዛፍ አየች፡፡ ፍሬዋም ጫፍ እስከ ጫፍ የሞላ ነበር፡፡ ጫፎቿም ምድርን የሚሸፍኑ ነበሩ፡፡ አንድ ሰው፣ ብርሃን ለብሶ ብርሃን ተጎናጽፎ፣ በእጁም ትምህርተ መስቀል ያላት የወርቅ ዘንግ ይዞ መጣ፡፡ ሁለት መሰላልም ይዞ መሰላሎቹን ከዛች ዛፍ ግራና ቀኝ አቆማቸው፡፡ ንግስት ሶፍያ ግን የዚህ ራእይ ምስጢር አልረዳ ቢላት ተጨነቀች፣ ምስጢሩን ይገልጽላት ዘንድም

Saturday, March 21, 2015

፮ተኛ ሳምንት ገብርኄር



ገብርኄር ማለት ቸር አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ይህንንም  በ ማቴ 25 ፥ 14-30 ላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የወንጌልን አደራ በምሳሌ እንዳስተማረ እንረዳለን፡፡ ትምህርቱ አንድ ባለጸጋ ሰው ነበረ ወደሩቅ ሀገር ለመሄድ ባሰበ ጊዜ አገልጋዮቹን ጠርቶ ከመንገዱ እስኪመለስ ድረስ ይሰራለት ዘንድ ለአንዱ አምስት፣ ለሁለተኛው ሁለት፣ ለሶስተኛው አንድ መክሊት (ታለንት) ሰጣቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት መክሊት በማትረፍ አስር መክሊት አደረገው፤ ሁለት መክሊት የተቀበለው  ወጥቶ ወርዶ እጥፍ አትርፎ  አራት አደረገው፡፡ ባለ አንዱ ግን ወደ ስራ ከመግባቱ በፊት በልቡ ውስጥ ስጋት፣ ጥርጣሬ፣ ፍርሀትንና አለማመንን ስላነገሰ ብሰራበት ቢጠፋብኝስ? ቢሰርቁኝስ? ቢቀሙኝስ? እያለ በማሰብ እሰራለሁ ብዬ ያለኝን ከማጣ ለምን ደብቄ  አስቀምጬ በመቆየት ሲመጣ የሰጠኝን አልመልስም ብሎ መክሊቱን  ቆፍሮ ቀበረው፡፡ ጊዜው ሲደርስ ባለንብረቱ መጣና አገልጋዮቹን ይተሳሰባቸው ጀመር፡፡

፮ተኛ ሳምንት ገብርኄር


   ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ሲሆን በዚህ ቀን ስለ ቅን አገልጋዮች ለአገልግሎት የሚያገለግሉበትን ጸጋ ለሰዎች ሁሉ የሚሰጥ “ወሀቤ ጸጋ” አገልጋዮቹን “ገብርኄር” እያለ ዋጋ የሚሰጥ አምላክ መሆኑ እየታሰበ ይመለካል፡፡


የእለቱ ስርዓተ አምልኮ
ዘቅዳሴ
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን                                 2ጢሞ 2 ፥ 1-16
በንፍቅ ዲያቆን                                      1 ጴጥ 5 ፥ 1-12
በንፍቅ ቄስ                                          የሐዋ 1 ፥ 6-9

ምስባክ፡-
                                 ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ፤
                                 ወሕግከኒ በማዕከለ ከርስየ፤
                                 ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ፡፡

አማርኛ ፡-                     አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለመናገር ወደድኩ                        
                                ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው
                                በታላቅ ጉባኤም ጽድቅህን አወራሁ (ተናገርኩ)፡፡

                                
ትርጉም፡-      አቤቱ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን (ህግህን፣ ወንጌልህን) እናገር ዘንድ ወደደኩ ህግህ በልቦናዬ ተጽፎ ይኖራል፣ ቸርነትህንም በብዙ ጉባኤ ነገርሁ፡፡

ወንጌል፡-       ማቴ 25 ፥ 14-31

ቅዳሴ፡-         የባስልዮስ ቅዳሴ

    

መጾም

ብጹዕ አቡነ ሺኖዳ ሣልሳዊ እነዳስተማሩት
ከዲን. በረከት ሐጎስ

ጾምን ጹመው የጾምን በረከት የማያገኙ ከጾም ጥቅምም የማይካፈሉ በከንቱ ይጾማሉ፡፡
ወርኃ ጾም የጥልቅ መንፈሳዊ ልምምድ ጊዜ ነው፡፡ ወደ እግዚአብሔር የምንቀርብበት ለእግዚአብሔር ያለንን ታላቅ ፍቅር የምናስመሰክርበት ወቅት ነው፡፡ ከዚህ ጥልቅ ፍቅረ እግዚአብሔር የተነሳ አንድ ጿሚ በስጋዊ አካሉ ላይ ይሰለጥናል፡፡ ከምድራዊ ምኞቶችና ስስቶች በላይ ይንሳፈፋል፡፡ ሰማይዊውን ያጣጥማል፡፡ ጾም ወደ አምላካችን የምንቀርብበት፣የምናውቅበት ብሎም ሰውነታችንን ስለ እግዚአብሔር የምንቀድስበት ዘመን ነው፡፡ ጾም የነፍስ እረፍት፤ የመንፈስ እርካታ የምናገኝበት ዲያቢሎስንም የምንዋጋበት የተቀደሰ ጊዜ ነው፡፡

የጾም ጊዜያት ከወትሮው በተለየ መልኩ ለመንፈሳዊ ኃይል የተሰጡ ናቸው፡፡ ገበሬ በመኸር ወራት አዘመራውን ሰብስቦ ከፊሉን ለገበያ ከፊሉን ለወርኃ ክረምት መቆያ እንደሚያከማች ሁሉ ክርስቲያኖችም በወርኃ ጾም በድካምና ጻማ የሚዘሩትን መንፈሳዊ አዝመራ የሚሰበስቡበት ወቅት ነው፡፡ የሚጾም ሰው በጾም ወራት መንፈሳዊ ኃይልና ብርታትን ከአምላኩ ይቀበላል፡፡   በእነዚህ የተቀደሱ ወራት የሚጎናጸፈው ኃይልም በፍስግ ቀናት ምርጉዝ ፣ ምቅዋም ይሆነዋል፡፡

Saturday, March 14, 2015

ደብረ ዘይት




ደብረ ዘይት ማለት የወይራ ዛፍ የበዛበት ተራራ ማለት ነው፡፡ ከኢየሩሳሌም በስተምስራቅ እንደምትገኝ ይነገራል፡፡ በዚህች ተራራ ሐዋርያት ስለ ዳግም ምጽአት ፣ ስለ ዓለም ህልፈት መቼና እንዴት እንደሆነ ይነግራቸው ዘንድ ጌታን ጠይቀውታል፡፡ የዘመኑ ፍፃሜ ሲቀርብ የሚታዩትን ምልክቶች በዝርዝር ነግሯቸዋል፡፡ (ማቴ 24 ፥ 1) በዚህ ሰንበትም ይህ ታሪክ የሚዘከርበት በመሆኑ ሳምንቱ በተራራው ስም ተሰይሟል፡፡

እንግዲህ በብሉይ ኪዳን  ዘመን ነቢየ እግዚአብሔር ቅዱስ ዳዊት ከአቤሴሎም በሸሸ ጊዜ የደብረ ዘይትን ተራራ ዐቀበት እንደወጣ (2ኛሳሙ 15 ፥ 30) ላይ እናነባለን፡፡ቤተ ፋጌና ቢታንያ የሚባሉት ታሪካውያን ቦታዎች ከደብረ ዘይት ግርጌ ይገኛሉ፡፡ መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የሆሳዕና ዕለት ከደብረ ዘይት ወደ ኢየሩሳሌም እንደ ገባ እናነባለን፡፡ ጌቴሴማኒ የሚባለው ጌታችን የጸለየበት ቦታ ከደብረ ዘይት ስር ይገኛል፡፡(ማቴ 26 ፥ 30-36) ጌታችን ወደ ሰማይ ያረገው በደብረ ዘይት ላይ ነው(ሉቃ 24 ፥ 1-52 ፣ ግ.ሐዋ 1 ፥ 12)፡፡ እግዲህ እነዚህ ሁሉ በቅዱስ መጽሐፍ ስለ ደብረ ዘይት የተነገሩ ናቸው፡፡ 

፭ተኛ ሳምንት ደብረ ዘይት





ስያሜው አንደቀደሙት ዕለታት ሁሉ የቅዱስ ያሬድ ስያሜ ሲሆን በዚህ ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ሁለተኛ በግርማ መለኮት በክበበ ትስብእት (በመለኮታዊ ግርማው በሰው መጠን)  እንደሚመጣ የዓለምም ፍፃሜው እንዴት እንደሚሆን ለሐዋርያት በደብረ ዘይት ማስተማሩን እንዲሁም በክብር ያረገው ጌታን ለሚጠባበቁ ዋጋቸውን፣ ላልተቀበሉትም ፍዳቸውን ሊከፍል የምድርን ስርዓት ሊሽር ሰማይን እና ምድርን አሳልፎ ለወዳጆቹ መንግስቱን ሊያወርስ፣ የቅዱሳኑንም እንባ ከአይናቸው ሊያብስ ፣ ኃጥአንን ሊወቅስ ፣ ፃድቃንን ሊያወድስ (ቡሩካን ብሎ) መምጣቱን እያሰበች ቤተ ክርስቲያን ፈጣሪዋን ታመልካለች፡፡

Friday, March 13, 2015

ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም


            

ደብረ ከዋክብት ዝቋላ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ አንድነት ገዳም 1168 .. ታላቁ ጻድቅ አቡነ ገብረ መንፈስ ቅዱስ በዚህ ዓለም በሕይወተ ሥጋ በነበሩበት ጊዜ ከግብጽ ወደ ኢትዮጵያ መጥተው ቅዱሳት በሆኑ እግሮቻቸው በመርገጥና በመባረክ በተራራው አናት ላይ በሚገኘው ውብና ማራኪ በሆነው ባሕር ውስጥ 1ዐዐ ዓመታት በመጸለይ ከዘለዓለማዊው አምላካችን ኢየሱስ ክርስቶስ የማይታበል ሕያው ቃል ኪዳን የተቀበሉበት 14ኛው መቶ ክፍለ ዘመን ከዚህ ዓለም በሞት ከተለዩ በኋላ ጽላታቸው የተቀረጸበት ቤተክርስቲያናቸው የታነጸበት በክቡር ስማቸው ገዳም የተመሠረተበት አምላከ ገብረ መንፈስ ቅዱስ ብርሃነ ረድኤቱን በየጊዜው የሚገልጥበት በሀገራችን ኢትዮጵያ አሉ ከሚባሉት ጥንታዊና ታሪካዊ ገዳማት አንዱ ነው፡፡

የዚህን ታላቅ ገዳም አመሠራረትና ታሪክ እንዲሁም መልክአ ምድር አቀማመጡን በመጠኑ ከዚህ እንደሚከተለው እናቀርባለን፡፡

በቅዳሴ ጊዜ የሚደረጉና የማይደረጉ ነገሮች


በቅዳሴ ጊዜ ስለሚደረጉና ሰለማይደረጉ ነገሮች  ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን እንደሚከተለው ያዛል!

በቅዳሴ ጊዜ የሚስቅ ሰው ቅዱስ ባስልዮስ በጻፈው በ፸፪ኛው አንቀጽ ካህን ቢሆን የሚያቀብል ነውና ሥጋ ወደሙን ከተቀበለና ካቀበለ በኋላ ወጥቶ አንድ ሱባዔ ይቀጣ ይጹም ይስገድ፣ የሳቀው ሕዝባዊ ቢሆን ግን ሥጋ ወደሙን ሳይቀበል ያን ጊዜ ፈጥኖ ይውጣ ይላል። ምነው ፍርድ አበላለጠ ካህኑን ተቀብሎ ወጥቶ ይቀጣ አለ፤ ሕዝባዊውን ሳይቀበል ወጥቶ ይሂድ አለ ቢሉ ካህኑ የሚቆመው ከውስጥ ነው ሲስቅ የሚያየው የለም። ካህኑ በቅዳሴ ጊዜ ቅዳሴውን ጥሎ ወጥቶ ሲሄድ ባዩት ጊዜ ቄስ እገሌ አባ እገሌ በመሥዋዕቱ ምን አይተውበታል ብለው መሥዋዕቱን ሳይቀር ይጠራጠሩታል፤ ስለዚህ ነው። ምዕመኑ ግን ሲስቅ ሁሉ ያየዋልና ለሌላ መቀጣጫ እንዲሆን፤ በቤተ መቅደስ የማይወደድ ሌላ ነገር አይናገር፤ በቤተ መቅደስ ጭንቅ፣ ደዌ ሳያገኘው አንዱን ስንኳ ምራቁን እንትፍ አይበል። ነገር ግን ደዌ ቢያስጨንቀው ድምፅ ሳያሰማ ምራቁን በመሐረቡ ተቀብሎ ያሽሸው።

በቤተ ክርስቲያንና በቅዳሴ ጊዜ ማንም ማን ዋዛ ፈዛዛ ነገር የሚናገር አይኑር፣ ቤተ ክርስቲያን በፈሪሃ እግዚአብሔር ሆነው የሚጸልዩባት