Monday, February 15, 2016

ተረፈ ካም

ካም ከሦስቱ የኖህ ልጆች ሁለተኛው ነው፡፡ ሴም ታላቅ ወንድሙ ያፌት ደግሞ ታናሹ፡፡ የጥፋት ውሃ ጎድሎ ምድርም ፈጽማ ከደረቀች በኋላ “አኀዘ ኖህ ይትገበራ ለምድር”  ኖህ ምድርን ይኮተኩታት ይቆፍራት ያርማት ጀመር፡፡ የወይን ሐረግም ተከለ፡፡ ከዚያው ከተከለው ወይን ጠጥቶ ሰከረ፡፡ በድንኳኑ ውስጥም ታራቆተ ፡፡


" ወርእዮ ካም አቡሁ ለከነዓን ዕርቃነ አቡሆሙ ሰሐቀ ወወፅአ ወነገሮሙ ለክልኤሆሙ አኃዊሁ በአፍአ" (የከነዓን አባት) ካምም የአባታቸውን ዕርቃን አይቶ ሳቀ፤ ተሳለቀ፡፡ ወደ ውጭ ወጥቶም ለሁለቱ ወንድሞቹ ነገራቸው፡፡ 

"ወነሥኡ ሴም ወያፌት ልብሰ ወወደዩ ላዕለ ዘባናቲሆሙ ወሖሩ ድኅሪተ ወከደኑ ዕርቃነ አቡሆሙ" ያፌትና ሴም ልብስ ወስደው ሁለቱም በትከሻቸው ላይ አደረጉ፡፡ የኋሊት ሄደው የአባታቸውን ዕርቃን ሸፈኑ፡፡ በዓይኖቻቸው የአባታቸውን እራቁትነት ለማየት እንኳን አልደፈሩም፡፡

"ወገፆሙ ድኅሬሆሙ አግብኡ ወኢርእዩ ዕርቃነ አቡሆሙ" ይላል፡፡ ፊታቸውን ወደ ኋላ አዙረው ወጡ፡፡ የአባታቸውን እርቃን አላዩም፡፡

ከዚህ በኋላ የወይን ስካር ፈጽሞ አእምሮ አይነሳምና ኖህ ከስካሩ ነቃ  ታናሹ ልጁ ካም እንደዘበተበት፤ ያፌትና ሴም ልባሳቸውን እንዳለበሱት ባወቀ ጊዜ በታናሹ ልጁ ካም አዘነበት፤

Monday, January 25, 2016

ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን

                                                 
    ቤተ ክርስቲያን ማለት ሕንፃው፣ የክርስቲያኖች አንድነት /ጉባኤ/ እና የምዕመኑ ሰውነት በመሆኑ ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን የምንለውም በእነዚህ በሦስቱ ላይ የተሠራውን ሥርዓት ነው። አንዳንዶቻችን ቤተ ክርስቲያንን ከራሳችን አርቀን ሌላ አካል አድርገን ስለምንመለከት ሥርዓቱ እኛን የሚመለከት አይመስለንም። ሥርዓቱ ግን የተሠራው ለሦስቱም የቤተ ክርስቲያን ትርጓሜዎች መሆኑን ማወቅ ተገቢ ነው።
  ሥርዓተ ቤተ ክርስቲያን ምንጩ ወይንም መሠረቱ መጽሐፍ ቅዱስ፣ የቅዱሳን አባቶቻችን ጉባኤያት ውሳኔ /ሲኖዶስ/ እና አባቶቻችን ሊቃውንት በተለያዩ ጊዜ ያደረጓቸው ጉባኤያት ውሳኔዎች ናቸው።

Monday, January 18, 2016




                         እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ!
 

                                    ገሃድ/ ጾመ ድራረ ጥምቀት

    
ገሃድ የቃሉ ትርጉም መገለጥ መታየት ነው፡፡ በጥምቀት መገለጥ መባሉ ሰው የሆነው አምላክ በዓለም ሲኖር እስከ 30 ዓመት እድሜው ድረስ ሰዎችን ለማዳን የመጣ መሲህ ሰው የሆነበት፣ አምላክ ኢየሱስ ክርስቶስ እሱ መሆኑን ሳያውቁ ከኖሩ በኃላ 30 ዓመት እድሜው በባሕረ ዮርዳኖስ በእደ ዮሐንስ እጅ ሲጠመቅ አብ በደመና ሆኖ ‹‹የምወደው ልጄ ይህ ነው›› በማለቱ መንፈስ ቅዱስ በርግብ አምሳል በራሱ ላይ ሲያርፍ በመታየቱ ነቢያት ይወርዳል ይወለዳል ይሰቀላል ይሞታል ይነሳል ብለው የተናገሩለት መሲሕ እርሱ መሆኑ ተገልጦአልና እንዲሁም ሦስቱ አካላት በአንድ ጊዜ ታይተዋልና ምስጢረ ሥላሴ የተገለጠለት በመሆኑ ገሃድ ይባላል፡፡(ማቴ 313-17)
ይህን በማሰብ የምንጾመው ጾምየገሃድ ጾምይባላል፡፡ ቀኑም ጥር 10 ቀን 11 አጥቢያ ነው፡፡ስለዚህ ጥር 10 ቀን ሰባቱ አጽዋማ አንዱ የሆነው የገሀድ ጾም ነው ማለት ነው!

ዚቅ ዘጥምቀት ወቃና ዘገሊላ

ውድ የጦማራችን ተከታታዮች እንኳን ለብርሃነ ጥምቀቱ በሰላም አደረሳችሁ እያልን ከሊቃውንቱ ጋር በመቆም ከበዓሉ በረከት ተካፈይ ትሆኑ ዘንድ ከከተራ በዓል (ከዋዜማው) ጀምሮ እስከ ቃና ዘገሊላ ድረስ ያለውን የማኅሌት ሥርዓት ከዚህ እንደሚከተለው  ከመጽሐፈ ዚቅ በማውጣት በጽሑፍ አቅርበንላችኋል።

ዋዜማ

ሃሌ ሉያ ኃዳፌ ነፍስ ለጻድቃን ወተስፋ ቅቡጻን፤
ክርስቶስ አስተርአየ ውስተ ዓለም፤
እምድንግል ተወልደ ክሡተ ኮነ፤
እንዘ ይትዔዘዝ ለአዝማዲሁ፤
ከዊኖ ሰብአ በዮርዳኖስ ተጠምቀ ፡፡

በሐምስተ

በዮርዳኖስ ተጠምቀ ፈጺሞ ሕገ፤
ወአስተርአየ ገሃደ በዮርዳኖስ ተጠምቀ፡፡

እግዚአብሔር ነግሠ

አስተርእዮ ኮነ ዘክርስቶስ ስነ መለኮት፤
ከመ ርግብ ውስተ ምጥማቃት እንዘ ይብል ዝንቱ ውእቱ ወልድየ ዘአፈቅር ፡፡

ይትባረክ
 

ርእዩከ ማያት እግዚኦ

Thursday, October 8, 2015

ዚቅ ወመዝሙር አመ ፴ ለመስከረም

  
 እንኳን ለዘመነ ጽጌ በሰላም አደረሳችሁ፡፡ በቤተክርስቲያናችን ዘመነ ጽጌን እና የእመቤታችንን ስደት አስመልክቶ ለሚቀጥሉት 6 እሑዶች (መስከረም ፴ ጥቅምት፯ ጥቅምት፲፬ ጥቅምት፳፩ ጥቅምት፳፰ ኅዳር፭) የሚቆመውን የማኅሌተ ጽጌ ዚቅና መዝሙር በየሳምንቱ ይዘንላችሁ እንቀርባለን::




ነግሥ ለኵልያቲክሙ...ዚቅ

ወኃይዝተ ወንጌል የዓውዳ ለቤተክርስቲያን፤
እም አርባዕቱ አፍላጋት፤
እንተ ትሰቀይ ትእምርተ ለለጽባሑ፤
እማቴዎስ ልደቶ ወእማርቆስ መንክራቶ፤
እም ሉቃስ ዜናዊ ተሰምዮ ወእም ዮሐንስ በግዓ፤
ወዘንተ ሰሚዓ ትገብር በዓለ በፍግዓ፤

ማኅሌተ ጽጌ

ጽጌ አስተርአየ ሠሪፆ እምዐፅሙ፤
ለዘአማኃኪ ጽጌ ለገብርኤል በይነ ሰላሙ፤
ወበእንተዝ ማርያም ሶበ ሐወዘኒ መዓዛ ጣዕሙ፤
ለተአምርኪ አኀሊ እሙ ማኅሌተ ጽጌ ዘይሰመይ ስሙ፤