Thursday, May 7, 2015

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ያስገነባው መንበረ ጵጵስና እና ጽ/ቤት ተመረቀ


001deb002deb
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገነባው ለመንበረ ጵጵስና እና ለጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል ባለ ሁለት ፎቅ ሕንፃ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሚያዝያ 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመረቀ፡፡

Wednesday, May 6, 2015

ስለትያትርና ኪነጥበብ ቅዱስ ዮሐንስ አፈወርቅ እነዳስተማረው

ከአቤል ተስፋዬ
በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አሐዱ አምላክ አሜን
…እንግዲህ (አብዝታችሁ) ብታነቡ የጌታችን ተከታይ ሆናችኋል፡፡ እርሱም ያነባ (ያለቅስ) ነበርና፤ በአልአዛር (መቃብር ላይ)፤ በከተማይቱ (ኢየሩሳሌምን) ላይ፤ ይሁዳም ባገኘው ጊዜ አብዝቶ አዝኖ ነበር፡፡ ብዙዎች ሲያዝን አይተውታል ነገር ግን ሲስቅም ሆነ ፈገግ ሲል ለቅጽበት ስንኳ በየትኛውም ጊዜ ያየው አንዳችም የለም፤ ከወንጌላውያኑ የትኛቸውም ይህን እንዳደረገ አልገለጹም፡፡ (ቅ.) ጳውሎስንም እንዲሁ፤ እንዳለቀሰ፤ ለሶስት አመታት ቀን ከሌሊት (ያለመቋረጥ) እንዳነባ ራሱም ገልጿል፤ ሌሎችም ስለርሱ ይህን መስክረዋል፤ እንደሳቀ ግን እርሱም የትም ቦታ ላይ አልጠቀሰም ከሌሎች ቅዱሳንም መካከል ይህን እንዳደረገ የተገለጸ ማንም የለም፤ ስለ ሳራ (የአብርሀም ሚስት) (እንደሳቀች) ተጠቅሷል ይኸውም (በሦስቱ መላዕክት) በተገሰጸችበት ወቅት ነበር፤ እንዲሁም የኖኸ ልጅ በተመሳሳይ ስለመሳቁ ተጽፏል፤ ይህን ባደረገበት ወቅት ግን (በአባቱ ተረግሟልና) ነጻነቱን በባርነት ለወጠ፡፡

እንዲህ የምላችሁ ሳቅ (ጨዋታ) የተባለን ሁሉ ለመኮነን አይደለም፤ አእምሯችሁ በከንቱነት እንዳይጠመድ ለማቀብ ነው እንጂ፤ እስኪ ልጠይቃችሁ በምቾት የምትንደላቀቁና በከንቱነት የተዘፈቃችሁ ሆናችሁ ሳለ በሚያስፈራው (የጌታችን) የፍርድ መንበር ፊት ቆማችሁ እዚህ (በምድር) ላይ ሳላችሁ ስለሰራችሁት ነገር አንድ በአንድ አትጠየቁምን? በእርግጥ እንጂ… ምክንያቱም አውቀን በድፍረት ስለሰራነውም ሆነ ከአቅማችን በላይ ሆኖብን ስለበደልነው በደል ምላሽ እንድንሰጥ እንጠየቃለንና… ‹‹ በሰዎች ፊት የሚክደኝን ሁሉ እኔ ደግሞ (በሰማዩ) አባቴ ፊት እክደዋለሁ›› ይላልና ጌታ፡፡ አለጥርጥር ማናችንም ጌታን ወደን አንክደውምና አውቀንና ፈቅደን አናደርገውም፤ ነገር ግን ይህም ቢሆን ከቅጣት አያድነንምና ይህንንም አስመልክቶ መልስ መስጠት ይኖርብናል፤ አውቀን ስለሰራነው ብቻ ሳይሆን ሳናውቅ የበደልነውም ጭምር ያስጠይቀናል፡፡ ‹‹ በራሴ አንዳች አላውቅም፤ ነገር ግን ይህ ምክንያት ሆኖኝ ከፍርድ አላመልጥም (አልድንም)›› ይላልና 1 ቆሮ 4፡4 ፤ደግሞም በሌላ ስፍራ እንዲህ ይላል ‹‹ ለእግዚአብሔር ቀናኢነት ያላቸው ናቸውና ይህን ቆጥሬላቸዋለሁ፤ ነገር ግን በእውቀት አይደለም›› ይሁን እንጂ ይህ በቂ ምክንያት ሆኖ አልተገኘም፡፡ ወደ ቆሮንጦስ ሰዎች በጻፈበት ወቅትም ደግሞ (ሐዋ. ቅ. ጳውሎስ) እንዲህ ብሏል ‹‹ እባቡ ሔዋንን በረቂቅ ተንኮሉ እንዳሳታት ሁሉ በጌታችን ካለ ቅንነት አእምሯችሁን እንዳይበርዘው እፈራለሁ››

Thursday, April 30, 2015

ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳፫



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አምላክ አመ ዕሥራ ወሠሉሱ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለተ ኮነ ፍጻሜ ስምዑ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዐቢይ ወክቡር ዘተሰምየ ፀሐየ ወኮከበ ጽባሕ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሚያዝያ ሃያ ሦስት በዚች ቀን ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ ሆነ፡፡

የዚህም ቅዱስ አባቱ መስፍን ነው፡፡ ስሙም አንስጣስዮስ ይባላል፡፡ ከቀጰዶቅያ አገር ነው፡፡ የእናቱም ስም ቴዎብስታ ይባላል ከፍልስጥዔም አገር ናት ታናሽ ሆኖ ሳለ አባቱ ዐረፈ፡፡



ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሔደ፡፡ ንጉሡም ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው፡፡

ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች፣ ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው፡፡

ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ፡፡ ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም፡፡

በሊቢያ በአይ ኤስ አይ ኤስ ስለተሰዉ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች የአኀት አብያተ ክርስቲያናት አባቶች መልዕክት

€œለገዳዮቹ ጸልዩ፤ ይቅርም በሏቸው፡፡€ /ብጹዕ አቡነ አንጄሎስ በኮፕት ኦርቶዶክስ የታላቋ ብርቲያንያ ሊቀ ጳጳስ/

001abune angeloአሸባሪው አይ ኤስ አይ ኤስ 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን መግደሉንና ለዚህም ሓላፊነቱን መውሰዱን ተናግሯል፡፡ ክርስቲያኖቹን በመግደሉ ይቅር እንለዋለን፤ እንጸልይለታለንም፡፡ በማለት ብፁዕ አቡነ አንጄሎስ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላላፈዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ አንጄሎስ አሸባሪው ቡድን በፈጸመው ድርጊት የተሰማቸውን ሐዘን ሲገልጹም €œአይ ኤስ አይ ኤስ በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ ክርስቲያኖቹን ሲሰዋቸው የሚያሳያውን ምስል ወድምጽ በሁለት ቅጂ በኢንተርኔት ለቋል፡፡ በለቀቀው ምስል ወድምጽም 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ተገድለዋል፡፡

Thursday, April 23, 2015

ሰማዕታቱ እና ሰማዕትነት




ሰማዕት የሚለው ቃል ከግዕዙ “ሰምዐ” ካለው የወጣ ነው፡፡ትርጉሙም መሰከረ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሰማዕት ላለው ቃል መነሻው ምስክር ማለት ነው፡፡“በኢየሩሳሌም ፣ በይሁዳ ፣በሰማርያ እሰከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” ሐዋ 1፥8-22 እንዳለው፡፡ እንግዲህ ምስክር የሚለው ቃል በመጀመሪያ ለሐዋርያት የተሰጠ ስም ሲሆን በኋላም ሀይማኖታቸውን እንደ ሐዋርያት ለሚገልጡ ምእመናን የተሰጠ ስያሜ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ደግሞ ምስክርነታቸውን የገለጡት በማስተማር ብቻ ሳይሆን ስለሚያስተምሩት ትምህርት(ወንጌል) ትክክለኛነት በፈቃዳቸው ሰማዕት እስከመሆን ደርሰው ነው፡፡ስለዚህ ሰማዕትነት ማለት ስለሃይማኖት ሲባል በፈቃድ ሞትን(መከራን) መቀበል ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ሰማዕትነት ሶስት ነገሮችን የያዘ ነው፡፡