Wednesday, May 20, 2015

ዕርገተ ክርስቶስ

ግንቦት12ቀን 2007ዓ.ም
በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ
አልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለመሕያው ዮሐ.3፥13
Ereget
ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ይህ ኃይለ ቃል ክብር ምስጋና ይግባውና ስለጌታችን፣ አምላካችን፣ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት መውረድ ከድንግል ማርያም መወለድ እና የሰውነቱን ሥራ ጨርሶ በክብር ወደ ሰማይ ማረጉን የሚገልጽ ነው፡፡ እንደሚታወቀው አምላካችን ስለሁለት ዐቢይ ጉዳዮች ሰው ሆኗል፡፡

Sunday, May 17, 2015

ዋዜማ ዘግንቦት ያሬድ


ዋዜማ
ንዑ ንትፈሣሕ በመኃልዪሁ ወንንግር ለካህን ውዳሴሁ፤
ከመ ሱራፌል ለያሬድ ክላሑ ለክርስቶስ ሰበከ ትንሳኤሁ፤
ማሕበረነ ይባርክ በእዴሁ፤
ምልጣን
ከመ ሱራፌል ለያሬድ ክላሑ ለክርስቶስ ሰበከ ትንሳኤሁ፤
ማሕበረነ ይባርክ በእዴሁ፤
ሃሌ ሉያ ንዑ ንትፈሣሕ በመኃልዪሁ ወንንግር ለካህን ውዳሴሁ፣
ያሬድ ጸሊ በእነቲአነ ጸሎትከ ወትረ ይብጽሐነ፤
ያሬድ ጸሊ በእንቲአነ፤
ያሬድ ማኅሌታይ ለእግዚአብሔር ካህኑ፤
ስብሐተ ትንሳኤ ዘይዜኑ፤
ኦሪት ቶታኑ ወወንጌል አሳእኑ፤
ትርድአነ ነአ በህየ መካኑ፤
ከመ ጸበል ግሑሳነ ጸርነ ይኩኑ፤
እለሰ ይዌድሱ ትንሳኤሁ ወይቄድሱ፣
ያሬድ ካህን ምስሌሆሙ ያንሶሱ፤
ሰላም
አንበሳ ዘሞአ ፍጹም ውእቱ፤
እምስርወ ዳዊት ወፈትሐ፤
መጽሐፈ ትምህርት፤
ያሬድ የሐሊ ትንሳኤሁ፤
ወለብሰ ሰላመ ዚአሁ፤

ዚቅ ዘግንቦት ያሬድ ዘይትበሃል በደብረ ይባቤ


ነግሥ
ሰላም ለአብ ገባሬ ኵሉ ዓለም፤
ለወልድ ሰላም ወለመንፈስ ቅዱስ ሰላም፤
ለማርያም ሰላም ወለመላእክት ሰላም፤
ሰላም ለነቢያት ወለሐዋርያት ሰላም፤
ለሰማዕታት ሰላም ወለጻድቃን ሰላም፤

ዚቅ
አብኒ የሐዩ ዘፈቀደ፤
ወልድኒ የሐዩ ዘፈቀደ፤
መንፈስቅዱስኒ የሐዩ ዘፈቀደ፤
እስመ በፈቃዱ ወለደነ በቃለ ጽድቁ፤
ወበተስፋ እንተ ባቲ ነሐዩ፤
እንተ ኪያሃ ይጸንሁ ጻድቃን፤
ሰላም ለቆምከ ጽዱለ ዋካ ወሞገስ
ሀበ መቃብሩ ዘቆመ ለበኵረ ትንሣኤ ክርስቶስ
ሚካኤል ሰዋኢ በግዐ ትንሣኤ ሠላስ፤
ኢይልሕቅ ወርኃ ምግብየ ከመ ሕዝቅያስ ንጉሥ፤
ፀሐየ ሕይወትየ አቅም በማዕረር ሐዲስ፤
ዚቅ
ቀዊሞ ገሐደ ውስተ አውደ ስምዕ፤
ያሬድ ሰበከ ትንሳኤ ሞቱ ለበግዕ፤
ሰላም ለዝክረ ስምኪ ዘመንክር ጣዕሙ፤
ለወልድኪ አምሳለ ደሙ፤
መሰረተ ሕይወት ማርያም ወጥንተ መድኃኒት ዘእምቀዲሙ፤
ኪያኪ ሰናይተ ዘፈጠረ ለቤዛ ዓለሙ፤
እግዚአብሔር ይትባረክ ወይትአኰት ስሙ፤
ዚቅ
ትውልደ ትውልድ ያስተበጽዕዋ፤
መላእክት በሰማያት እኅትነ ይብልዋ፤
ፍሬ ማኅፀና ለማርያም ቤዘወ ፄዋ፤
ወአግብኦሙ ውስተ ርስቶሙ ለአዳም ወለሔዋ፤
ሰላም ዕብል ለያሬድ ቀሲስ፤
ለኢትዮጵያ ነደቃ በሃሌ ሉያ ምድራስ፤
አስተካልሐ በውዳሴ በዜማ ሠላስ፤
በመሐልይሁ ሐዋዝ ወስብሐት ሐዲስ፤

Monday, May 11, 2015

የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ተጠናቀቀ



ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም.
ሚያዝያ 27 ቀን 2007 ዓ.ም. ከቀኑ 10፡00 ሰዓት በጸሎት የተጀመረው የርክበ ካህናት ቅዱስ ሲኖዶስ ምልዓተ ጉባኤ ሲካሔድ ቆይቶ  ሚያዝያ 30 ቀን 2007 ዓ.ም. ረፋድ ላይ ተጠናቅቆ የሚከተለውን መግለጫ ሰጥቷል፡፡

Thursday, May 7, 2015

የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት ያስገነባው መንበረ ጵጵስና እና ጽ/ቤት ተመረቀ


001deb002deb
የሰሜን ሸዋ ሀገረ ስብከት በደብረ ብርሃን ከተማ ያስገነባው ለመንበረ ጵጵስና እና ለጽ/ቤት አገልግሎት የሚውል ባለ ሁለት ፎቅ ሕንፃ በብፁዕ ወቅዱስ አቡነ ማትያስ ፓትርያርክ ርዕሰ ሊቃነ ጳጳሳት ዘኢትዮጵያ ሊቀ ጳጳስ ዘአክሱም ወእጨጌ ዘመንበረ ተክለ ሃይማኖት ሚያዝያ 25 ቀን 2007 ዓ.ም. ተመረቀ፡፡