Saturday, March 28, 2015

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ




ኒቆዲሞስ ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ የአይሁድ አለቃ እና መምህር ነበረ “ወሀሎ አሐዱ ብእሲ እምፈሪሳውያን ዘስሙ ኒቆዲሞስ መልአኮሙ ለአይሁድ” ዮሐ3÷1 እንዲል፡፡ ሳምንቱ (ሰንበቱ) በእርሱ የተሰየመበት ዋናው ምክንያት ይህ ሰው በሌሊት እየመጣ ምስጢረ ጥምቀትን፣ ዳግም ልደትን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ እግር ስር ቁጭ ብሎ የተማረበት ቀን መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም ትምህርቱ ጌታችን ዋና የሆነውን እና ሰው ከውሀ እና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግስት እንደማይገባ በግልጽ አስተምሮታል፡


ኒቆዲሞስ ከቀን ይልቅ በሌሊት መማርን ስለምን መረጠ? 


ኒቆዲሞስ ይህንን ያደረገው ስለሶስት ነገር እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይናገራሉ ያስተምራሉ፡፡

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ

ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ በዚህ እለት የፈሪሳውያን አለቃ ኒቆዲሞስ በሌሊት ወደ ጌታ መጥቶ ሲማር ጌታም ምስጢረ ጥምቀትን ዳግም ልደትን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው እየጠቀሰ ቅዱስ ያሬድ ዮሐ 3 ላይ ያለውን ወንጌል ስለዘመረው የእለቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ተብሏል፡፡


በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን ፡-                 ሮሜ 7፥ 1-19   
በንፍቅ ዲያቆን፡-                       1ዮሐ 4፥18-ፍጻሜ
በንፍቅ ቄስ ፡-                          የሐዋ 5፥ 34
ምስባክ፡-        


ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ፤
አመከርከነ ወኢተረክበ ዐመጻ በላዕሌየ፤
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፡፡

አማርኛ ፡-                


ልቤን ፈተንከው በሌሊትም ጎበኘኸኝ፤
ፈተንከኝ ምንም አላገኘህብኝም፤
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው፡፡


ወንጌል:-           ዮሐ 3 ፥1-20
ቅዳሴ:-            ቅዳሴ ማርያም

Wednesday, March 25, 2015

አብርሃ ወአጽብሐ

ቅዱሳን ነገስታት አብርሃ ወአጽብሐ አባታቸው ታዜር እናታቸው ሶፍያ/አህየዋ/ በቅድስና የሚኖሩ እግዚአብሔርን በቅድስና በንጽህና የሚያገለግሉ ነገር ግን ልጅ ያላገኙ መካኖች ነበሩ። ስለሆነም ጌታ ሆይ ደስ የሚያሰኝህ በትዕዛዝህም የሚኖር ልጅ ስጠን እያሉ እግዚአብሔርን ይለምኑ ነበር፡፡

ከዕለታት አንድ ቀን ስለ እግዚአብሔር ቸርነት ሲነጋገሩ ንግስት ሶፍያ የሐና እመ ሳሙኤልን ጸሎት በመጥቀስ እሷም እንደ ሐና ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን እንድትለምን ንጉሱን ጠየቀችው፡ ንጉሱም “ ኦ ብእሲቶ ሰናየ ኁለይኪ” አንቺ ሆይ መልካም አስበሻል በማለት በምክሯ ተስማምቶ ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን በጸሎት እንድትጠይቅ ፈቀደላት፡፡ ንግስት ሶፍያም የካቲት 18 ቀን ሱባኤ ገብታ ፈጣሪዋን መለመን ጀመረች፡፡ ከጸሎቷም ጥቂቱ “ በኪሩቤል ላይ የምትኖር፣ የቀለያትንም (ጥልቅ ባህርንም) የምትመለከት ጌታዬ ፈጠሪዬ ሆይ አቤቱ ጸሎቴንና ልመንያን ስማኝ፣ ልቅሶየንም አድምጥ ቸላ አትበለኝ” የሚል ነበር፡፡

ደጓ ንግስት ሶፍያ በብዙ ጸሎትና እንባ ሱባኤዋን ለመጨረስ ስትቃረብ፣ አንድ ራእይ ተገለጠላት፣ እሱም ከተራራ ላይ የተተከለች ረዥም ዛፍ አየች፡፡ ፍሬዋም ጫፍ እስከ ጫፍ የሞላ ነበር፡፡ ጫፎቿም ምድርን የሚሸፍኑ ነበሩ፡፡ አንድ ሰው፣ ብርሃን ለብሶ ብርሃን ተጎናጽፎ፣ በእጁም ትምህርተ መስቀል ያላት የወርቅ ዘንግ ይዞ መጣ፡፡ ሁለት መሰላልም ይዞ መሰላሎቹን ከዛች ዛፍ ግራና ቀኝ አቆማቸው፡፡ ንግስት ሶፍያ ግን የዚህ ራእይ ምስጢር አልረዳ ቢላት ተጨነቀች፣ ምስጢሩን ይገልጽላት ዘንድም

Saturday, March 21, 2015

፮ተኛ ሳምንት ገብርኄር



ገብርኄር ማለት ቸር አገልጋይ ማለት ነው፡፡ ይህንንም  በ ማቴ 25 ፥ 14-30 ላይ ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ የወንጌልን አደራ በምሳሌ እንዳስተማረ እንረዳለን፡፡ ትምህርቱ አንድ ባለጸጋ ሰው ነበረ ወደሩቅ ሀገር ለመሄድ ባሰበ ጊዜ አገልጋዮቹን ጠርቶ ከመንገዱ እስኪመለስ ድረስ ይሰራለት ዘንድ ለአንዱ አምስት፣ ለሁለተኛው ሁለት፣ ለሶስተኛው አንድ መክሊት (ታለንት) ሰጣቸው፡፡ አምስት መክሊት የተቀበለው ወጥቶ ወርዶ ሌላ አምስት መክሊት በማትረፍ አስር መክሊት አደረገው፤ ሁለት መክሊት የተቀበለው  ወጥቶ ወርዶ እጥፍ አትርፎ  አራት አደረገው፡፡ ባለ አንዱ ግን ወደ ስራ ከመግባቱ በፊት በልቡ ውስጥ ስጋት፣ ጥርጣሬ፣ ፍርሀትንና አለማመንን ስላነገሰ ብሰራበት ቢጠፋብኝስ? ቢሰርቁኝስ? ቢቀሙኝስ? እያለ በማሰብ እሰራለሁ ብዬ ያለኝን ከማጣ ለምን ደብቄ  አስቀምጬ በመቆየት ሲመጣ የሰጠኝን አልመልስም ብሎ መክሊቱን  ቆፍሮ ቀበረው፡፡ ጊዜው ሲደርስ ባለንብረቱ መጣና አገልጋዮቹን ይተሳሰባቸው ጀመር፡፡

፮ተኛ ሳምንት ገብርኄር


   ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ሲሆን በዚህ ቀን ስለ ቅን አገልጋዮች ለአገልግሎት የሚያገለግሉበትን ጸጋ ለሰዎች ሁሉ የሚሰጥ “ወሀቤ ጸጋ” አገልጋዮቹን “ገብርኄር” እያለ ዋጋ የሚሰጥ አምላክ መሆኑ እየታሰበ ይመለካል፡፡


የእለቱ ስርዓተ አምልኮ
ዘቅዳሴ
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን                                 2ጢሞ 2 ፥ 1-16
በንፍቅ ዲያቆን                                      1 ጴጥ 5 ፥ 1-12
በንፍቅ ቄስ                                          የሐዋ 1 ፥ 6-9

ምስባክ፡-
                                 ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ፤
                                 ወሕግከኒ በማዕከለ ከርስየ፤
                                 ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ፡፡

አማርኛ ፡-                     አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለመናገር ወደድኩ                        
                                ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው
                                በታላቅ ጉባኤም ጽድቅህን አወራሁ (ተናገርኩ)፡፡

                                
ትርጉም፡-      አቤቱ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን (ህግህን፣ ወንጌልህን) እናገር ዘንድ ወደደኩ ህግህ በልቦናዬ ተጽፎ ይኖራል፣ ቸርነትህንም በብዙ ጉባኤ ነገርሁ፡፡

ወንጌል፡-       ማቴ 25 ፥ 14-31

ቅዳሴ፡-         የባስልዮስ ቅዳሴ