Saturday, March 28, 2015

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ

ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ በዚህ እለት የፈሪሳውያን አለቃ ኒቆዲሞስ በሌሊት ወደ ጌታ መጥቶ ሲማር ጌታም ምስጢረ ጥምቀትን ዳግም ልደትን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው እየጠቀሰ ቅዱስ ያሬድ ዮሐ 3 ላይ ያለውን ወንጌል ስለዘመረው የእለቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ተብሏል፡፡


በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን ፡-                 ሮሜ 7፥ 1-19   
በንፍቅ ዲያቆን፡-                       1ዮሐ 4፥18-ፍጻሜ
በንፍቅ ቄስ ፡-                          የሐዋ 5፥ 34
ምስባክ፡-        


ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ፤
አመከርከነ ወኢተረክበ ዐመጻ በላዕሌየ፤
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፡፡

አማርኛ ፡-                


ልቤን ፈተንከው በሌሊትም ጎበኘኸኝ፤
ፈተንከኝ ምንም አላገኘህብኝም፤
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው፡፡


ወንጌል:-           ዮሐ 3 ፥1-20
ቅዳሴ:-            ቅዳሴ ማርያም