ኢትዮጵያ የእመቤታችን ቅድስት
ድንግል
ማርያም
የአሥራት
አገር
ናት፡፡
ሊቃውንትም
ነቢያት
የተነበዩትን
ትንቢት
የቆጠሩትን
ሱባዔ
መሠረት
በማድረግ
ቅድስት
ድንግል
ማርያም
በኪደተ
እግሯ
ኢትዮጵያን
መባረኳን
ያስተምራሉ፡፡
«ነቢዩ
ዕንባቆም
የኢትዮጵያ
ድኳኖች
ሲጨነቁ
ዐየሁ፤»
ዕንባ.
3፡7
ብሎ
የተናገረው
ቃለ
ትንቢት
እመቤታችን
የኢትዮጵያን
አውራጃዎች
ለመባረኳ
ማስረጃ
መሆኑን
ሊቃውንተ
ቤተ
ክርስቲያን
ይተረጉማሉ፤
ያመሠጥራሉ፡፡
ኢየሱስ
ክርስቶስ ኢትዮጵያን ለእናቱ አሥራት አድርጐ በመሥጠቱ በእርሷ በኩል ለሰው ልጆች ሁሉ የሚሆን የነገረ ድኅነት ምሥጢር
በመከናወኑ ኢትዮጵያውያን ለእመቤታችን ቅድስት ድንግል ማርያም የተለየ ፍቅር አለን፡፡ የአብነት /የቆሎ/ ተማሪዎች በትምህርት
ዓለም ከአንዱ ወደሌላው እየተዘዋወሩ /የአብነት/ ትምህርት ሲማሩ በእንተ ስማ ለማርያም፤ ስለማርያም እያሉ፡፡ የእመቤታችን ስም
ስንቅ ምግብ ሆኗቸው ይጠቀሙበታል፡፡ ግሼን ደብረ ከርቤ የልጇ ግማደ መስቀል ከከተመበት አምባም የሚጓዙ ምእመናን «አንድ እፍኝ
ሽምብራ አልያዝኩም ከቤቴ ስሟ ስንቅ ነው የእመቤቴ» እያሉ በፍቅሯ ተማርከው ግብር ሰፍረው ዕጣን ቋጥረው ሱባዔ እየገቡ
ይማፀኗታል፡፡