Thursday, April 23, 2015

ሰማዕታቱ እና ሰማዕትነት




ሰማዕት የሚለው ቃል ከግዕዙ “ሰምዐ” ካለው የወጣ ነው፡፡ትርጉሙም መሰከረ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሰማዕት ላለው ቃል መነሻው ምስክር ማለት ነው፡፡“በኢየሩሳሌም ፣ በይሁዳ ፣በሰማርያ እሰከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” ሐዋ 1፥8-22 እንዳለው፡፡ እንግዲህ ምስክር የሚለው ቃል በመጀመሪያ ለሐዋርያት የተሰጠ ስም ሲሆን በኋላም ሀይማኖታቸውን እንደ ሐዋርያት ለሚገልጡ ምእመናን የተሰጠ ስያሜ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ደግሞ ምስክርነታቸውን የገለጡት በማስተማር ብቻ ሳይሆን ስለሚያስተምሩት ትምህርት(ወንጌል) ትክክለኛነት በፈቃዳቸው ሰማዕት እስከመሆን ደርሰው ነው፡፡ስለዚህ ሰማዕትነት ማለት ስለሃይማኖት ሲባል በፈቃድ ሞትን(መከራን) መቀበል ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ሰማዕትነት ሶስት ነገሮችን የያዘ ነው፡፡

Monday, April 20, 2015


ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ መግለጫ ሰጠ
                   
ሚያዚያ 12/2007
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሊቢያ በአሸባሪው አይሲስ እጅ በሰማዕትነት የተሠውትን ኢትዮጵያውያን በተመለከተ ዛሬ ጠዋት 5፡30 ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ከውጭ ሀገር ጉዞ ቀርተው በመንበረ ፓትርያርኩ የቅዱስ ሲኖዶሱን መግለጫ የሰጡ ሲሆን ሌሎች የእምነት ተቋማትም ተመሳሳይ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
መግለጫውን ተመልከቱት፡፡
  ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዐረፉ           
002abune peteros 
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የባሕር ዳር፤ የአዊና የመተከል አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ሚያዝያ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ጠዋት ዐርፈዋል፡፡

ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. በባሕር ዳር ከተማ የተገነባውን መንፈሳዊ ኮሌጅ በቅዱስ ፓትርያርኩ ካስመረቁ በኋላ ድንገት በመታመማቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደው ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆይም ሚያዝያ 10 ቀን ጠዋት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ሥርዐተ ቀብራቸው እሁድ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡

Wednesday, April 15, 2015

የትንሣኤው ትርጉምና የሰሙነ ፋሲካ ዕለታት

                     ትንሣኤ የሚለው ቃል የግእዝ ቋንቋ ነው፡፡

             መገኛ ቃሉም ተንሥአ =  ተነሣ የሚለው ግሥ ይሆናል፡፡
ትንሣኤ ማለት = መነሣት፣ አነሣሥ፤ ሐዲስ ሕይወት ማግኘት ማለትን ያመለክታል፡፡ ትንሣኤ በሊቃውንተ ቤተ ክርስቲያን በየመልኩ፣ በየዐይነቱ ሲተረጐም አምስት ክፍሎች አሉት፡፡
አንደኛው ትንሣኤ ኅሊና ነው፡፡ ይህም ማለት ተዘክሮተ እግዚአብሔር ነው፡፡
ሁለተኛውም ትንሣኤ ልቡና ነው፡፡ የዚህም ምስጢሩ ቃለ እግዘብሔርን መስማትና በንስሐ እየታደሱ በሕይወት መኖር ነው፡፡
ሦስተኛው ትንሣኤ ለጊዜው የሙታን በሥጋ መነሣት ይሆናል፡፡ ነገር ግን ድጋሚ ሞት ይከተለዋል፡፡
አራተኛውትንሣኤ የክርስቶስ በገዛ የባሕርይ ሥልጣኑ ሞትን ድል አድርጎ መነሣት ነው፡፡ የትምህርታችንም መሠረት ይኸው ነው፡፡
ዐምስተኛውና የመጨረሻው የትንሣኤ ደረጃም የባሕርይ አምላክ የጌታችን የመድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስን ትንሣኤ መሠረት ያደረገ ትንሣኤ ዘጉባኤ ነው፡፡ ይህም ከዓለም ኅልፈት በኋላ ሰው ሁሉ እንደየሥራው ለክብርና ለውርደት፣ ለጽድቅና ለኩነኔ በአንድነት የሚነሣው የዘለዓለም ትንሣኤ ይሆናል፡፡

Wednesday, April 8, 2015

በሰሙነ ሕማማት የሚነሡ ጥያቄዎችና መልሶቻቸውአትምኢሜይል
መጋቢት 29 ቀን 2007 ዓ.ም.

በኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በዓዋጅ ከሚጾሙት አጽዋማት መካከል ዐቢይ ጾም፤ ጾመ ኢየሱስ አንዱና ዋነኛው ነው፡፡ አሁን በጾሙ መጨረሻ ሳምንት የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስን ሕማምና ሥቃይ እንዲሁም እንግልት በምናስብበትና የጨለማውን ዘመን በምናስታውስበት ጊዜ /ሰሙነ ሕማማት/ ላይ እንገኛለን፡፡

ስለ ሰሙነ ሕማማት ስናነሣ በምእመናን ዘንድ የሚነሡ አንዳንድ ጥያቄዎች አሉ፡፡ እኛም እነዚህን ጥያቄዎች ለሊቃውንተ ቤተክርስቲያን በማቅረብ የሰጡንን ምላሽ ይዘን ቀርበናል፡፡