የሰሙነ ሕማማት ሃይማኖታዊና ቱፊታዊ ክንዋኔዎች
በዐቢይ ጾም ከሰርክ ሆሳዕና ጀምሮ እስከ ትንሳኤ ሌሊት ያሉት ዕለታት የሚገኙበት ሳምንታት ሰሙነ ሕማማት ይባላል፡፡ ዕለታቱም የዓመተ ፍዳ፣ የዓመተ ኩነኔ መታሰቢያ ናቸው፡፡ በእነዚህ ዕለታት ውስጥ የተለያዩ ትውፊታዊ እና ሃይማኖታዊ ክንዋኔዎች አሉ፡፡ ከነዚህ ክንዋኖዎች ውስጥ አለመሳሳም፣ አክፍሎት፣ ቄጤማ ማሰር፣ ጥብጠባ፣ ጉልባን እና ሕፅበተ እግር ይገኙበታል፡፡ ስለእነዚህ ክንዋኔዎች በቅድስት ቤተ ክስቲያን ስላለው ትውፊታዊ አፈፃፀም መዛግብት አገላብጠን እንደሚከተለው አቅርበናል፡፡
አለመሳሳም፡- በሰሙነ ሕማማት የኦርቶዶክስ ተዋህዶ እምነት ተከታዮች መስቀል እንደማይሳለሙት ሁሉ መጨባበጥ፣ መሳሳምን የትክሻ ሰላምታ መለዋወጥን አይፈጽሙም፡፡ ሰላምታ የማንለዋወጥበት ምክንያት አይሁድ ጌታን ለመስቀል ሰኞ እና ማግሰኞ መከሩ አልሰመረላቸውም፡፡ ምክረቸው የተፈጸመው ረቡዕ ነው፡፡ ስለዚህ አይሁድ እያንሾካሾኩ እንሰቀለው ፤እንግለው ብለው ይማከሩ ነበር፡፡ በዘመነ ፍዳ ወቅት ሠላምና ፍቅር አለመኖሩን የሚገልፅልን በመሆኑ ያንን ለማስታወስ ስላምታ አንለዋወጥም፡፡ መስቀልም አንሳለምም፡፡ ሳምንቱ የክፋት ምክር የተመከረበት እንጂ የፍቅርና የደስታ ሳምንት የታየበት ባለመሆኑ ይህንን በማሰብ ሰላምታ አንለዋወጥም፡፡ አይሁዳ ጌታን በጠላቶቹ ለማስያዝ እኔ የምስመው እርሱ ነው ያዙት ብሎ በሰላምታው ምልክት ሰጣቸው ይህ ሰላምታ አምሐ ቅድሳት አይደለም ተንኮል የተሞለበት እንጂ፡፡ የዲያቢሎስም ሰላምታ ተመሳሳይ ነው፡፡ ሔዋንን ስላም ለኪ ብሎ ነው ያታለላት የይሁዳም ሰላምታ ሰይጣናዊ ነው፡፡ ስለዚህ ይህንን ወቅትና ሁኔታ ለማሰብ በሰሙነ ሕማማት ሰለምታ ልውውጥ የለም፡፡ ዛሬ እየተስተዋለ ያለው ይኽው ሰላምታ ያለመለዋወጥ ሁኔታ ስርወ መሰረቱ ይህ ነው፡፡ ከጥንት ጀምሮ እዚህ ትውልድ ላይ ደርሷል፡፡ ይቀጥላልም፡፡ |
Saturday, April 4, 2015
ሰሙነ ሕማማት
እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና በሰላም አደረሳችሁ!!
የሆሳዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩስአሌም ሲገባ የሚቀድሙት እና የሚከተሉት ህዝብ በተለይም አእሩግ እና ህጻናት “ሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሳዕና በአርያም “ በማለት ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው።
ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው። |
Wednesday, April 1, 2015
ዚቅ ወመዝሙር ዘሆሣዕና
ነግስ
ሰላም እብል ለዘዚአክሙ ቆም፡፡
ዓለማተ ዓለም ሥላሴ ዘአልብክሙ ዓለም፡፡
እምኔክሙ አሐዱ በእንተ ፩ዱ አዳም፡፡
እመኒ በምድር ተወክፎ ለነግደ ጲላጦስ ሕማም፡፡
ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም፡፡
ዚቅ
እም ሆሣዕናሁ አርአየ ተአምረ ወመንክረ፤
ዘኢተገብረ እምቅድመዝ፤
መልክአ ኢየሱስ ለዝክረ ስምከ…ዚቅ
ሆሣዕና በአርያም ለወልደ ዳዊት ለንጉሠ እስራኤል፤
ዘይሁብ ዝናመ ተወን ከመ ትካት ይመልዕ ዓውደ
እክል፤
በረከተ ምክያዳተ ወይን
ለመትከፍትከ…ዚቅ
ኢይብክያ ዘከልዓ ደናግለ፤
አርዑተ መስቀል ፆረ፤
እስከ ቀራንዮስ ሖረ፤
ኢይብክያ ዘከልዓ ደናግለ፤
ለአእጋሪከ…ዚቅ
ኦ አእጋር እለ አንሶሰዋ ውስተ ገነት፤
ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል
ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል
መዝሙር
ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ፣
ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ
ወእነዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ
ጽድቅ፤
ኀበ ደብረዘይት ሙራደ ዐቀብ ሀገረ እግዚአብሔር፤
ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት፤
ነሲኦሙ አእፁቀ በቀልት፤
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፤
ተጽኢኖ ዲበ እዋል ቦኣ ሀገረ ኢየሩሳሌም፤
በትፍሥሕት ወበሐሤት ይሁቦሙ ኃይለ ወስልጣነ፤
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፤
ተጽኢኖ ዲበ እዋል ቦኣ ሀገረ ኢየሩሳሌም ፤
በትፍሥሕት ወበሐሤት ይሁቦሙ ኃይለ ወስልጣነ፤
ወስብሐት ለእግዚአብሔር
Monday, March 30, 2015
ከሞት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ /ክፍል ፩/
እንደምን ሰነበታችሁ ውድ ክርስቲያኖች? . . . እስቲ አንዲት ጥያቄ ልጠይቃችሁ?
ሞትን ታውቁታላችሁ?
እኔማ አሁን ባለፈው ዕለት እንዳጋጣሚ አገኘሁት እና እባክህ ቃለ መጠይቅ ላድርግህ ብዬ ብጠይቀው
አሻፈረኝ አለ፡፡ ብለው ብሰራው . . . ወይ ፍንክች!!! "ኧረ ባክህ እንደው
ለአጭር ሰዓት ላስቸግርህ?" እሱ መቼ ሰምቶኝ፡፡
በመጨረሻም "በዮሐንስ አፈወርቅ?" ብዬ ስለምነው "ያኔ አስራ ሁለት
አመት ገትሮ አቁሞኛል፡፡ አሁን ደግሞ ሃያ አራት ዓመት ያደርግብኝ እንደሆነ መከራ ታሳየኛለህ፡፡" አለና እሺ አለኝ፡፡
እኔም የነገረኝን በማስታወሻዬ ፃፍኩት፡፡ ይኸው አሁን በክፍል በክፍል እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌ ለእናንተ እንደሚከተለው አቀረብኩት
. . .
ጥያቄ፡- ስለትውልድህ እና እድገትህ ብታጫውተኝ?
Subscribe to:
Posts (Atom)