Showing posts with label ዐቢይ_ጾም. Show all posts
Showing posts with label ዐቢይ_ጾም. Show all posts

Wednesday, April 1, 2015

ዚቅ ወመዝሙር ዘሆሣዕና


ነግስ
ሰላም እብል ለዘዚአክሙ ቆም፡፡
ዓለማተ ዓለም ሥላሴ ዘአልብክሙ ዓለም፡፡
እምኔክሙ አሐዱ በእንተ ፩ዱ አዳም፡፡
እመኒ በምድር ተወክፎ ለነግደ ጲላጦስ ሕማም፡፡
ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም፡፡


ዚቅ
እም ሆሣዕናሁ አርአየ ተአምረ ወመንክረ፤
ዘኢተገብረ እምቅድመዝ፤
ወኢይከውን እምድኅረዝ፤



መልክአ ኢየሱስ ለዝክረ ስምከዚቅ
ሆሣዕና በአርያም ለወልደ ዳዊት ለንጉሠ እስራኤል፤
ዘይሁብ ዝናመ ተወን ከመ ትካት ይመልዕ ዓውደ እክል፤
በረከተ ምክያዳተ ወይን






ለመትከፍትከዚቅ
ኢይብክያ ዘከልዓ ደናግለ፤
አርዑተ መስቀል ፆረ፤
እስከ ቀራንዮስ ሖረ፤
ኢይብክያ ዘከልዓ ደናግለ፤

ለአእጋሪከዚቅ
ኦ አእጋር እለ አንሶሰዋ ውስተ ገነት፤
ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል

መዝሙር
ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ፣
ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ
ወእነዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ፤
ኀበ ደብረዘይት ሙራደ ዐቀብ ሀገረ እግዚአብሔር፤
ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት፤
ነሲኦሙ አእፁቀ በቀልት፤
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፤
ተጽኢኖ ዲበ እዋል ቦኣ ሀገረ ኢየሩሳሌም፤
በትፍሥሕት ወበሐሤት ይሁቦሙ ኃይለ ወስልጣነ፤

ምልጣን
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፤
ተጽኢኖ ዲበ እዋል ቦኣ ሀገረ ኢየሩሳሌም ፤
በትፍሥሕት ወበሐሤት ይሁቦሙ ኃይለ ወስልጣነ፤





ወስብሐት ለእግዚአብሔር




Saturday, March 28, 2015

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ

ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ በዚህ እለት የፈሪሳውያን አለቃ ኒቆዲሞስ በሌሊት ወደ ጌታ መጥቶ ሲማር ጌታም ምስጢረ ጥምቀትን ዳግም ልደትን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው እየጠቀሰ ቅዱስ ያሬድ ዮሐ 3 ላይ ያለውን ወንጌል ስለዘመረው የእለቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ተብሏል፡፡


በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን ፡-                 ሮሜ 7፥ 1-19   
በንፍቅ ዲያቆን፡-                       1ዮሐ 4፥18-ፍጻሜ
በንፍቅ ቄስ ፡-                          የሐዋ 5፥ 34
ምስባክ፡-        


ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ፤
አመከርከነ ወኢተረክበ ዐመጻ በላዕሌየ፤
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፡፡

አማርኛ ፡-                


ልቤን ፈተንከው በሌሊትም ጎበኘኸኝ፤
ፈተንከኝ ምንም አላገኘህብኝም፤
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው፡፡


ወንጌል:-           ዮሐ 3 ፥1-20
ቅዳሴ:-            ቅዳሴ ማርያም

Saturday, March 21, 2015

፮ተኛ ሳምንት ገብርኄር


   ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ሲሆን በዚህ ቀን ስለ ቅን አገልጋዮች ለአገልግሎት የሚያገለግሉበትን ጸጋ ለሰዎች ሁሉ የሚሰጥ “ወሀቤ ጸጋ” አገልጋዮቹን “ገብርኄር” እያለ ዋጋ የሚሰጥ አምላክ መሆኑ እየታሰበ ይመለካል፡፡


የእለቱ ስርዓተ አምልኮ
ዘቅዳሴ
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን                                 2ጢሞ 2 ፥ 1-16
በንፍቅ ዲያቆን                                      1 ጴጥ 5 ፥ 1-12
በንፍቅ ቄስ                                          የሐዋ 1 ፥ 6-9

ምስባክ፡-
                                 ከመ እንግር ፈቃደከ መከርኩ አምላኪየ፤
                                 ወሕግከኒ በማዕከለ ከርስየ፤
                                 ዜኖኩ ጽድቀከ በማኅበር ዐቢይ፡፡

አማርኛ ፡-                     አምላኬ ሆይ ፈቃድህን ለመናገር ወደድኩ                        
                                ሕግህም በልቤ ውስጥ ነው
                                በታላቅ ጉባኤም ጽድቅህን አወራሁ (ተናገርኩ)፡፡

                                
ትርጉም፡-      አቤቱ አምላኬ ሆይ ፈቃድህን (ህግህን፣ ወንጌልህን) እናገር ዘንድ ወደደኩ ህግህ በልቦናዬ ተጽፎ ይኖራል፣ ቸርነትህንም በብዙ ጉባኤ ነገርሁ፡፡

ወንጌል፡-       ማቴ 25 ፥ 14-31

ቅዳሴ፡-         የባስልዮስ ቅዳሴ

    

Saturday, March 14, 2015

፭ተኛ ሳምንት ደብረ ዘይት





ስያሜው አንደቀደሙት ዕለታት ሁሉ የቅዱስ ያሬድ ስያሜ ሲሆን በዚህ ቀን ጌታችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ  ሁለተኛ በግርማ መለኮት በክበበ ትስብእት (በመለኮታዊ ግርማው በሰው መጠን)  እንደሚመጣ የዓለምም ፍፃሜው እንዴት እንደሚሆን ለሐዋርያት በደብረ ዘይት ማስተማሩን እንዲሁም በክብር ያረገው ጌታን ለሚጠባበቁ ዋጋቸውን፣ ላልተቀበሉትም ፍዳቸውን ሊከፍል የምድርን ስርዓት ሊሽር ሰማይን እና ምድርን አሳልፎ ለወዳጆቹ መንግስቱን ሊያወርስ፣ የቅዱሳኑንም እንባ ከአይናቸው ሊያብስ ፣ ኃጥአንን ሊወቅስ ፣ ፃድቃንን ሊያወድስ (ቡሩካን ብሎ) መምጣቱን እያሰበች ቤተ ክርስቲያን ፈጣሪዋን ታመልካለች፡፡

Saturday, March 7, 2015

፬ተኛ ሳምንት መጻጕዕ




መጻጕዕ ማለት ድውይ በሽተኛ  ማለት ነው፡፡ ሳምንቱ በዚህ የተሰየመበት ዋናው ምክንያት በ ዮሐ 5÷1-9 እንደተፃፈው ለሠላሣ ስምንት ዓመታት በደዌ ዳኛ በአልጋ ቁራኛ ተይዞ ይኖር የነበረ በሽተኛን ጌታችን አምላካችን መድሐኒታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ በተአምር የፈወሰበት  ሰንበት መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡ይህ ድውይ የፀናበት ሰው በእብራይስጥ ቤተሳይዳ ወደምትባል መጠመቂያ ቦታ የሚወስደው ወገንና ዘመድ አጥቶ በመጠመቂያ አካባቢ   ለ38 ዓመት በአልጋው ላይ እንደተኛ ቆይቷል፡፡ ማዳን የባሕሪው የሆነው ጌታችን አምላካችን መድሐኒታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ ግን በአንድ ቃል  “ተነስና አልጋህን ተሸክመህ ሂድ” ብሎ ፈውሶታል፡፡ ነገር ግን “ተነስና ሂድ” ከማለቱ በፊት “መዳን ትወዳለህን?” ብሎ መልካም ምኞቱን ጠይቆታል፡፡ ለምን? መዳን ወዳለሁ ብሎ እንደሚመልስለት ያውቅ የለምን ስለምን እንዲህ ብሎ ጠየቀው? ይህም አላዋቂ የነበረን ስጋ እንደ ተዋሐደ ለማጠየቅ  እንዲህ ሲል ጠይቆታል፡፡ ድውዩም መዳን እወድ ነበር ነገር ግን ወደጸበሉ ተሸክሞ የሚያደርሰኝ የለም በማለት ብቸኝነቱን ተናግሯል፡፡ አባባሉም ጌታችን አምላካችን መድሐኒታችን  ኢየሱስ ክርስቶስ በወቅቱ የሠላሣ ዓመት ወጣት ስለነበረ ተሸክሞ ወደ ጠበሉ ያደርሰኛል አልያም ብዙ ተከታዮች ስለነበሩት አንዱን ያዝልኛል ብሎ በማሰብ ነው፡፡ምክንያቱም አምላክነቱን ፣ ሁሉን ቻይነቱን አያውቅም ነበርና፡፡

Saturday, February 28, 2015

3ተኛ ሳምንት ምኵራብ



ምኩራብ የአይሁድ ቤተ ጸሎት ነው፡፡ ምኵራብ ማለትም ሰቀላ መሰል አዳራሽ ማለት ነው። አይሁድ ስግደትና መሥዋዕታቸውን የሚያቀርቡት በኢየሩሳሌም ባለው መቅደስ ብቻ ነው ብለው ቢያምኑም (ዮሐ 420) ፤በየተበተኑበት ቦታ ምኩራብ እየሠሩ ትምህርተ ኦሪትን በመማር ሃይማኖታቸውን ያፀኑ ነበር። ከአስር በላይ አይሁዳውያን በአንድ መንደር  ካሉ  አንድ ምኵራብ  እንዲሰራላቸው የአይሁድ ህግ ያዛልአይሁድ በምኲራቦቻቸው የሕግንና የነቢያትን መጻሕፍት /የብራና ጥቅሎች/ በአንድ ሣጥን ውስጥ ያስቀምጣሉ፡፡ በመሆኑ የጸሎት ሥፍራዎቻቸውን ለትምህርትና ለአምልኮ ይጠቀሙባቸዋል፡በምኩራብ አይሁድ ይጸልያሉ፣ ይማራሉ፣ ያስተምራሉ በአጠቃላይ ስርዓተ አምልኮን ይፈጽማሉ፡፡ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚያ ምራብ ለማስተማር በገባ ጊዜ ግን በተቃራኒው መሸጫ እና መለወጫ ሆነው ርግብንና በሬን ሲነግዱ እንደነበረ ተጽፏል፡፡ጌታችንም ይህንን አይቶ እንደፈለጋችሁ ሁኑ ብሎ ዝም አላላቸውም፡፡

Saturday, February 21, 2015

ሁለተኛ ሳምንት - ቅድስት



የካቲት ፲፬ ፳፻፯ ዓ.ም

የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋሕዶ ቤተ ክርስቲያን በሥርዓትና በትውፊት የበለፀገች መሆኗ የታመነ ነው፡፡ ሰፊ ሥርዓትና ትውፊት ያላት እንደመሆኗ መጠን የምታከብረው ሰንበትና በዓል፤ የምትጾመው ጾም፤ የምትጸልየው ጸሎት፤ የምትቆመው ማኅሌት በቂ ታሪክ፣ ትውፊትና ሥርዓት አለው፡፡ ያለታሪክ ያለትውፊትና ሥርዓት ቤተ ክርስቲያናችን የምትጸልየው ጸሎት፤ የምትጾመው ጾም፤ የምታከብረው ሰንበትና በዓል፤ የምትዘምረውም መዝሙር የለም፡፡


በዚህ በያዝነው ወቅት የምንጾመው ጾም የጌታችን የመድኃኒታችን የኢየሱስ ክርስቶስ ጾም እንደመሆኑ መጠን በዚሁ የጾም ወራት ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በዚህ ዓለም በዘመነ ሥጋዌው ለሠራቸው የተአምራትና የትምህርት ሥራዎች መታሰቢያ በዓል በማድረግ ለእያንዳንዱ ሰንበት ስም በመስጠት በስሙ አንፃር የበዓሉን ታሪክ በመከተል ታመሰግናለች፤ ትዘምራለች፤ ትፀልያለች፤ ትቀድሳለች፡፡
የቅድስት ቤተ ክርስቲያንን መዝሙር ንባቡን ከዜማው አስማምቶና አጠናቅሮ የተናገረው ሊቁ ቅዱስ ያሬድ በጾመ ድጓው በዓቢይ ጾም ውስጥ  ለሚገኙት እሑዶች ሁሉ የተለየ መዝሙር ሰርቶላቸዋል፡፡ በመዝሙራቱ ውስጣዊ ምስጢር መሠረትም እያንዳንዱ እሑድ ስያሜ ተሰጥቶቸል፡፡ በዚሁም መሠረት ያሳለፍነውን ሳምንት ከቅበላው ዋዜማ ጀምሮ ዘወረደ ብለን በቤተ ክርስቲያናችን አክብረናል፡፡ በቀደመው ጽሑፋችንም የስያሜውን ትርጓሜ አይተናል፡፡ ለዛሬ ደግሞ እንደእግዚአብሔር መልካም ፍቃድ የቀጣዩን ሰንበት/ሳምንት (የሁለተኛውን ሳምንት) ስያሜና ምሥጢሩን እንማማራለን፡፡ 


Sunday, February 15, 2015

ዐቢይ ፆም እና የዐቢይ ፆም ሳምንታት ስያሜ /ክፍል አንድ/






ከቃሉ ስንነሳ ‹‹ዐቢይ ፆም›› ማለት ዋና ፆም፣ የአፅዋማት ሁሉ የበላይ ፆም ማለት ነው፡፡ ይህንንም ስያሜውን ያገኘው ራሱ ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ፵(አርባ) መዓልት ፵(አርባ) ሌሊት የፆመውን ፆም በማሰብ የሚጾም ስለሆነ ነው(ማቴ ፬፥፩)፡፡ ፆሙን አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ብቻ ስለምን አደረገው ቢሉ ቀድሞ አባቶቻችን ነቢያት አርባ መዓልት አርባ ሌሊት ፁመዋልና ከዚያ አትርፎ ቢጾም አተረፈ፤ ቢያጎድል አጎደለ የአባቶቻችንንም ሥርዐት አፈረሰ ብለው አይሁድ  ሕገ ወንጌልን ከመቀበል በተከለከሉ ነበርና ነው፡፡

እንግዲህ በዚህ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ጌታችን አምላካችን መድኃኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ሦስቱን አርእስተ ኃጣውእ (አርእስተ ኃጣውእ የሚባሉት ትዕቢት፣ ስስት እና ፍቅረ ንዋይ ናቸው) ድል አድርጎበታል፡፡አንድም ሙሴ በአርባ ዘመኑ ለዕብራዊ ረድቶ ግብፃዊውን ገድሎ በኆፃ ቀብሮታል፡፡ሙሴ የወልደ እግዚአብሔር፤ ዕብራዊ የአዳም፤ ግብፃዊው የዲያብሎስ፤ ኆፃ የመስቀል ምሳሌ  አንድም የሦስቱ አርእስተ ኃጣውእ ምሳሌ ነው፡፡ ሙሴ አርባ መዓልትና አርባ ሌሊት ጹሞ ህገ ኦሪትን ሠርቷል