Tuesday, June 30, 2015

ጸሎተ ፍትሐት ምንድ ነው? ለምንስ ይጠቅማል?
 

 
ሰኔ 23 ቀን 2007 ዓ.ም.
ፍትሐት ማለት ከዚህ ዓለም በሞት ለሚለዩ ሰዎች በሕይወተ ሥጋ ሳሉ ከሠሩትና ከፈጸሙት በደል እንዲነጹ ከማእሠረ ኃጢአት እንዲፈቱ ወደ እግዚአብሔር የሚቀብ ጸሎት ነው፡፡ ቤተ ክርስቲያን ለሙታን ጸሎተ ፍትሐት እንዲደረግ ታዝዛለች፡፡
ጸሎተ ፍትሐት ለበደሉት ሥርየት ኃጢአትን፣ ይቅርታን ዕረፍተ ነፍስን ያሰጣል፡፡ ለደጋጎች ደግሞ ክብርን፣ ተድላን፣ ዕረፍትን ያስገኛል፡፡

Friday, May 29, 2015

                                የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ አትጥራ!

የእግዚአብሔርን ስም በከንቱ መጥራት ሲባል ምን ማለት ነው? የአምላካችን የእግዚአብሔር ስም የከበረ በመሆኑ እንደተገኘ የሚጠሩት፣ እንደአጋጠመ የሚናገሩት አይደለም፡፡ ይልቁንም በመፍራትና በመንቀጥቀጥ በትሕትና ሆነው ሊጠሩት የሚገባ ክቡር ስም ነው፡፡ ይሁን እንጂ አንዳንድ ሰዎች የእግዚአብሔርን ስም ያለአግባብ በነገራቸው ሁሉ ውስጥ ሲያስገቡት፣ ሥፍራም ጊዜም ሳይመርጡ እንደፈለጉት ሲጠሩት ይስተዋላሉ፡፡ እንደዚህ ዓይነት ሰዎች እምነትና ፊሪሃ እግዚአብሔር አላቸው ለማለት አያስደፍርም፤ ምክንያቱም የሚያምኑና
 
ከዚህ ቀጥለን ሰዎች ስሙን በከንቱ የሚጠሩባቸውን ሁኔታዎች ባጭር ባጭሩ ለመመልከት እንሞክራለን፡፡

Tuesday, May 26, 2015


                                      ተዋሕዶ-በደም


በደም ተመሥርተሽ
በደም ተገንብተሸ
በደም ተዋሕደሽ
በደም ተሰራጭተሸ

Wednesday, May 20, 2015

ዕርገተ ክርስቶስ

ግንቦት12ቀን 2007ዓ.ም
በመ/ር ምሥጢረ ሥላሴ ማናየ
አልቦ ዘዓርገ ውስተ ሰማይ ዘእንበለ ዘወረደ እምሰማይ ወልደ ዕጓለመሕያው ዮሐ.3፥13
Ereget
ከሰማይ ከወረደው የሰው ልጅ በቀር ወደ ሰማይ የወጣ የለም፡፡ እርሱም በሰማይ የሚኖረው ነው፡፡ ይህ ኃይለ ቃል ክብር ምስጋና ይግባውና ስለጌታችን፣ አምላካችን፣ መድኀኒታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ከሰማየ ሰማያት መውረድ ከድንግል ማርያም መወለድ እና የሰውነቱን ሥራ ጨርሶ በክብር ወደ ሰማይ ማረጉን የሚገልጽ ነው፡፡ እንደሚታወቀው አምላካችን ስለሁለት ዐቢይ ጉዳዮች ሰው ሆኗል፡፡

Sunday, May 17, 2015

ዋዜማ ዘግንቦት ያሬድ


ዋዜማ
ንዑ ንትፈሣሕ በመኃልዪሁ ወንንግር ለካህን ውዳሴሁ፤
ከመ ሱራፌል ለያሬድ ክላሑ ለክርስቶስ ሰበከ ትንሳኤሁ፤
ማሕበረነ ይባርክ በእዴሁ፤
ምልጣን
ከመ ሱራፌል ለያሬድ ክላሑ ለክርስቶስ ሰበከ ትንሳኤሁ፤
ማሕበረነ ይባርክ በእዴሁ፤
ሃሌ ሉያ ንዑ ንትፈሣሕ በመኃልዪሁ ወንንግር ለካህን ውዳሴሁ፣
ያሬድ ጸሊ በእነቲአነ ጸሎትከ ወትረ ይብጽሐነ፤
ያሬድ ጸሊ በእንቲአነ፤
ያሬድ ማኅሌታይ ለእግዚአብሔር ካህኑ፤
ስብሐተ ትንሳኤ ዘይዜኑ፤
ኦሪት ቶታኑ ወወንጌል አሳእኑ፤
ትርድአነ ነአ በህየ መካኑ፤
ከመ ጸበል ግሑሳነ ጸርነ ይኩኑ፤
እለሰ ይዌድሱ ትንሳኤሁ ወይቄድሱ፣
ያሬድ ካህን ምስሌሆሙ ያንሶሱ፤
ሰላም
አንበሳ ዘሞአ ፍጹም ውእቱ፤
እምስርወ ዳዊት ወፈትሐ፤
መጽሐፈ ትምህርት፤
ያሬድ የሐሊ ትንሳኤሁ፤
ወለብሰ ሰላመ ዚአሁ፤