Thursday, April 30, 2015

ስንክሳር ዘሚያዝያ ፳፫



በስመ አብ ወወልድ ወመንፈስ ቅዱስ አምላክ አመ ዕሥራ ወሠሉሱ ለሚያዝያ በዛቲ ዕለተ ኮነ ፍጻሜ ስምዑ ለቅዱስ ጊዮርጊስ ሰማዕት ዐቢይ ወክቡር ዘተሰምየ ፀሐየ ወኮከበ ጽባሕ፡፡

አንድ አምላክ በሚሆን በአብ በወልድ በመንፈስ ቅዱስ ስም ሚያዝያ ሃያ ሦስት በዚች ቀን ፀሐይና የአጥቢያ ኮከብ የተባለ ታላቅና ክቡር የሆነ የሰማዕቱ የቅዱስ ጊዮርጊስ የምስክርነት ፍጻሜ ሆነ፡፡

የዚህም ቅዱስ አባቱ መስፍን ነው፡፡ ስሙም አንስጣስዮስ ይባላል፡፡ ከቀጰዶቅያ አገር ነው፡፡ የእናቱም ስም ቴዎብስታ ይባላል ከፍልስጥዔም አገር ናት ታናሽ ሆኖ ሳለ አባቱ ዐረፈ፡፡



ሃያ ዓመትም በሆነው ጊዜ የአባቱን ሹመት ሊቀበል ወደ ንጉሥ ዱድያኖስ ዘንድ ሔደ፡፡ ንጉሡም ጣዖትን እንዲአመልኩ ሰዎችን ሁሉ ሲያስገድዳቸው አገኘው፡፡

ይህንንም አይቶ ቅዱስ ጊዮርጊስ እጅግ አዘነ በእርሱ ዘንድ ያለውን ገንዘቡን ሁሉ ለድኆች፣ ለምስኪኖች ሰጠ ባሮቹንም ነፃ አወጣቸው፡፡

ከዚህ በኋላ በንጉሥ ፊት ቁሞ በክብር ባለቤት በጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ ታመነ፡፡ ንጉሡም አባበለው ብዙ ቃል ኪዳንም ገባለት እርሱ ግን አልተቀበለውም፡፡

በሊቢያ በአይ ኤስ አይ ኤስ ስለተሰዉ ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች የአኀት አብያተ ክርስቲያናት አባቶች መልዕክት

€œለገዳዮቹ ጸልዩ፤ ይቅርም በሏቸው፡፡€ /ብጹዕ አቡነ አንጄሎስ በኮፕት ኦርቶዶክስ የታላቋ ብርቲያንያ ሊቀ ጳጳስ/

001abune angeloአሸባሪው አይ ኤስ አይ ኤስ 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖችን መግደሉንና ለዚህም ሓላፊነቱን መውሰዱን ተናግሯል፡፡ ክርስቲያኖቹን በመግደሉ ይቅር እንለዋለን፤ እንጸልይለታለንም፡፡ በማለት ብፁዕ አቡነ አንጄሎስ አባታዊ መልእክታቸውን አስተላላፈዋል፡፡

ብፁዕ አቡነ አንጄሎስ አሸባሪው ቡድን በፈጸመው ድርጊት የተሰማቸውን ሐዘን ሲገልጹም €œአይ ኤስ አይ ኤስ በሊቢያ በአሰቃቂ ሁኔታ ክርስቲያኖቹን ሲሰዋቸው የሚያሳያውን ምስል ወድምጽ በሁለት ቅጂ በኢንተርኔት ለቋል፡፡ በለቀቀው ምስል ወድምጽም 30 ኢትዮጵያውያን ክርስቲያኖች ተገድለዋል፡፡

Thursday, April 23, 2015

ሰማዕታቱ እና ሰማዕትነት




ሰማዕት የሚለው ቃል ከግዕዙ “ሰምዐ” ካለው የወጣ ነው፡፡ትርጉሙም መሰከረ ማለት ነው፡፡ ስለዚህ ሰማዕት ላለው ቃል መነሻው ምስክር ማለት ነው፡፡“በኢየሩሳሌም ፣ በይሁዳ ፣በሰማርያ እሰከ ዓለም ዳርቻ ድረስ ምስክሮቼ ትሆናላችሁ” ሐዋ 1፥8-22 እንዳለው፡፡ እንግዲህ ምስክር የሚለው ቃል በመጀመሪያ ለሐዋርያት የተሰጠ ስም ሲሆን በኋላም ሀይማኖታቸውን እንደ ሐዋርያት ለሚገልጡ ምእመናን የተሰጠ ስያሜ ነው፡፡ ቅዱሳን ሐዋርያት ደግሞ ምስክርነታቸውን የገለጡት በማስተማር ብቻ ሳይሆን ስለሚያስተምሩት ትምህርት(ወንጌል) ትክክለኛነት በፈቃዳቸው ሰማዕት እስከመሆን ደርሰው ነው፡፡ስለዚህ ሰማዕትነት ማለት ስለሃይማኖት ሲባል በፈቃድ ሞትን(መከራን) መቀበል ማለት ነው፡፡ በዚህም ምክንያት ሰማዕትነት ሶስት ነገሮችን የያዘ ነው፡፡

Monday, April 20, 2015


ቅዱስ ሲኖዶስ ዛሬ መግለጫ ሰጠ
                   
ሚያዚያ 12/2007
የኢትዮጵያ ቤተ ክርስቲያን ቅዱስ ሲኖዶስ በሊቢያ በአሸባሪው አይሲስ እጅ በሰማዕትነት የተሠውትን ኢትዮጵያውያን በተመለከተ ዛሬ ጠዋት 5፡30 ላይ መግለጫ ሰጥቷል፡፡ ብጹዕ ወቅዱስ ፓትርያርክ አቡነ ማትያስ ከውጭ ሀገር ጉዞ ቀርተው በመንበረ ፓትርያርኩ የቅዱስ ሲኖዶሱን መግለጫ የሰጡ ሲሆን ሌሎች የእምነት ተቋማትም ተመሳሳይ መግለጫ ይሰጣሉ ተብሎ እየተጠበቀ ነው፡፡
መግለጫውን ተመልከቱት፡፡
  ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ ዐረፉ           
002abune peteros 
ብፁዕ አቡነ ጴጥሮስ የባሕር ዳር፤ የአዊና የመተከል አኅጉረ ስብከት ሊቀ ጳጳስ በተወለዱ በ84 ዓመታቸው ሚያዝያ 10 ቀን 2007 ዓ.ም. ጠዋት ዐርፈዋል፡፡

ሐሙስ ሚያዝያ 8 ቀን 2007 ዓ.ም. በባሕር ዳር ከተማ የተገነባውን መንፈሳዊ ኮሌጅ በቅዱስ ፓትርያርኩ ካስመረቁ በኋላ ድንገት በመታመማቸው ወደ ሆስፒታል ተወስደው ሕክምና ሲደረግላቸው ቢቆይም ሚያዝያ 10 ቀን ጠዋት ከዚህ ዓለም በሞት ተለይተዋል፡፡

ሥርዐተ ቀብራቸው እሁድ ሚያዝያ 11 ቀን 2007 ዓ.ም. በባሕር ዳር ፈለገ ገነት ቅዱስ ጊዮርጊስ ካቴድራል ተፈጸመ፡፡