Friday, March 6, 2015

ልብ ብለው ያንብቡት!

             
ከእለታት ባንድቀን አባት የሚጠባ ልጁን እንዲጠብቅለት ከውሻው ጋር ትቶት ወደ አደን ይሄዳ።  ከአደን ሲመለስ ውሻውን በደም ተጨማልቆ በሩ ላይ አገኘው። ውሻው የተጨማለቀበትን ደም ሲመለከት ልጁን በልቶት እንደሆነ ገመተ። ልክ ሁላችንም እንደምንገምተው በጣም ተናዶ ለአደን ይዞት የነበረውን መሳሪያ አቀባበለና ውሻውን የጥይት ሩምታ አወረደበት።የተረፉ የልጁን አካል ለማየት ወደ ውስጥ እየሮጠ ገባ። ነገር ግን ልጁ አንዳችም መጥፎ ነገርአላገኘውም። ይልቁንስ ከፊትለፊት በደም የተጨማለቀ ተኩላ ሞቶ ተመለከተ።ተመልከቱ ስሜቱ ሸፍኖት የዕድሜ ልክ ፀፀት የሆነበት ስራ ፈፀመ!!!። ስንቶቻችን ነገሮችን ሳናረጋግጥ ከብዙዎች
ተቆራርጠናል?  ልልህ የፈለኩት አንተ የሰው ልጅ ሆይ! ፊትለፊት በምታይበት አይንህ ብቻ አትፍረድ! አዕምሮህንም ለፍርዱ ሹመት ስጠው! በችኮላ ስህተትን ሰርተህ ህይወትህን በሙሉ የሚፀፅትህ ነገር ውስጥ እንዳትገባ ተጠንቀቅ!!!።

No comments:

Post a Comment