Saturday, April 4, 2015

እንኳን ለበዓለ ሆሳዕና በሰላም አደረሳችሁ!!





የሆሳዕና በዓል ጌታችን ኢየሱስ ክርስቶስ በአህያ ጀርባ ተቀምጦ ወደ ኢየሩስአሌም ሲገባ የሚቀድሙት እና የሚከተሉት ህዝብ በተለይም አእሩግ እና ህጻናትሆሳዕና ለዳዊት ልጅ በጌታ ስም ሚመጣ የተባረከ ነው፤ ሆሳዕና በአርያምበማለት ጌታችንን መቀበላቸው የሚታወስበት በዓል ነው።
ሆሣዕና ከስምንቱ የዐቢይ ጾም እሑዶች አንዱና የመጨረሻው ሳምንት ተብሎ የሚጠራው ከትንሣኤ ቀድሞ የሚገኝ የሕማማት መግቢያ ዋዜማ ነው።

Wednesday, April 1, 2015

ዚቅ ወመዝሙር ዘሆሣዕና


ነግስ
ሰላም እብል ለዘዚአክሙ ቆም፡፡
ዓለማተ ዓለም ሥላሴ ዘአልብክሙ ዓለም፡፡
እምኔክሙ አሐዱ በእንተ ፩ዱ አዳም፡፡
እመኒ በምድር ተወክፎ ለነግደ ጲላጦስ ሕማም፡፡
ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም ሆሣዕና በአርያም፡፡


ዚቅ
እም ሆሣዕናሁ አርአየ ተአምረ ወመንክረ፤
ዘኢተገብረ እምቅድመዝ፤
ወኢይከውን እምድኅረዝ፤



መልክአ ኢየሱስ ለዝክረ ስምከዚቅ
ሆሣዕና በአርያም ለወልደ ዳዊት ለንጉሠ እስራኤል፤
ዘይሁብ ዝናመ ተወን ከመ ትካት ይመልዕ ዓውደ እክል፤
በረከተ ምክያዳተ ወይን






ለመትከፍትከዚቅ
ኢይብክያ ዘከልዓ ደናግለ፤
አርዑተ መስቀል ፆረ፤
እስከ ቀራንዮስ ሖረ፤
ኢይብክያ ዘከልዓ ደናግለ፤

ለአእጋሪከዚቅ
ኦ አእጋር እለ አንሶሰዋ ውስተ ገነት፤
ተቀነዋ በቅንዋተ መስቀል

መዝሙር
ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ፣
ሃሌ ሉያ፣ ሃሌ ሉያ
ወእነዘ ሰሙን በዓለ ፋሲካ ቀርቡ አርዳኢሁ ለአምላከ ጽድቅ፤
ኀበ ደብረዘይት ሙራደ ዐቀብ ሀገረ እግዚአብሔር፤
ወተቀበልዎ ሕዝብ ብዙኃን አዕሩግ ወሕፃናት፤
ነሲኦሙ አእፁቀ በቀልት፤
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፤
ተጽኢኖ ዲበ እዋል ቦኣ ሀገረ ኢየሩሳሌም፤
በትፍሥሕት ወበሐሤት ይሁቦሙ ኃይለ ወስልጣነ፤

ምልጣን
እንዘ ይብሉ ሆሣዕና በአርያም፤
ተጽኢኖ ዲበ እዋል ቦኣ ሀገረ ኢየሩሳሌም ፤
በትፍሥሕት ወበሐሤት ይሁቦሙ ኃይለ ወስልጣነ፤





ወስብሐት ለእግዚአብሔር




Monday, March 30, 2015

ከሞት ጋር የተደረገ ቃለ መጠይቅ /ክፍል ፩/



እንደምን ሰነበታችሁ ውድ ክርስቲያኖች? . . . እስቲ አንዲት ጥያቄ ልጠይቃችሁ?
ሞትን ታውቁታላችሁ?
እኔማ አሁን ባለፈው ዕለት እንዳጋጣሚ አገኘሁት እና እባክህ ቃለ መጠይቅ ላድርግህ ብዬ ብጠይቀው አሻፈረኝ አለ፡፡ ብለው ብሰራው . . . ወይ ፍንክች!!! "ኧረ ባክህ እንደው ለአጭር ሰዓት ላስቸግርህ?" እሱ መቼ ሰምቶኝ፡፡
በመጨረሻም "በዮሐንስ አፈወርቅ?" ብዬ ስለምነው "ያኔ አስራ ሁለት አመት ገትሮ አቁሞኛል፡፡ አሁን ደግሞ ሃያ አራት ዓመት ያደርግብኝ እንደሆነ መከራ ታሳየኛለህ፡፡" አለና እሺ አለኝ፡፡ እኔም የነገረኝን በማስታወሻዬ ፃፍኩት፡፡ ይኸው አሁን በክፍል በክፍል እንደሚሆን እንደሚሆን አድርጌ ለእናንተ እንደሚከተለው አቀረብኩት . . .

ጥያቄ፡-   ስለትውልድህ እና እድገትህ ብታጫውተኝ?

Saturday, March 28, 2015

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ




ኒቆዲሞስ ከፈሪሳውያን ወገን የሆነ የአይሁድ አለቃ እና መምህር ነበረ “ወሀሎ አሐዱ ብእሲ እምፈሪሳውያን ዘስሙ ኒቆዲሞስ መልአኮሙ ለአይሁድ” ዮሐ3÷1 እንዲል፡፡ ሳምንቱ (ሰንበቱ) በእርሱ የተሰየመበት ዋናው ምክንያት ይህ ሰው በሌሊት እየመጣ ምስጢረ ጥምቀትን፣ ዳግም ልደትን ከጌታችን ከመድኃኒታችን ከኢየሱስ ክርስቶስ እግር ስር ቁጭ ብሎ የተማረበት ቀን መታሰቢያ ስለሆነ ነው፡፡ በዚህም ትምህርቱ ጌታችን ዋና የሆነውን እና ሰው ከውሀ እና ከመንፈስ ካልተወለደ በቀር ወደ እግዚአብሔር መንግስት እንደማይገባ በግልጽ አስተምሮታል፡


ኒቆዲሞስ ከቀን ይልቅ በሌሊት መማርን ስለምን መረጠ? 


ኒቆዲሞስ ይህንን ያደረገው ስለሶስት ነገር እንደሆነ ሊቃውንተ ቤተክርስቲያን ይናገራሉ ያስተምራሉ፡፡

፯ተኛ ሳምንት ኒቆዲሞስ

ስያሜው የቅዱስ ያሬድ ነው፡፡ በዚህ እለት የፈሪሳውያን አለቃ ኒቆዲሞስ በሌሊት ወደ ጌታ መጥቶ ሲማር ጌታም ምስጢረ ጥምቀትን ዳግም ልደትን ለኒቆዲሞስ እንዳስተማረው እየጠቀሰ ቅዱስ ያሬድ ዮሐ 3 ላይ ያለውን ወንጌል ስለዘመረው የእለቱ ስያሜ ኒቆዲሞስ ተብሏል፡፡


በቅዳሴ ጊዜ የሚነበቡ የመጽሐፍ ቅዱስ ክፍሎች
በገባሬ ሰናይ ዲያቆን ፡-                 ሮሜ 7፥ 1-19   
በንፍቅ ዲያቆን፡-                       1ዮሐ 4፥18-ፍጻሜ
በንፍቅ ቄስ ፡-                          የሐዋ 5፥ 34
ምስባክ፡-        


ሐወጽከኒ ሌሊተ ወፈተንኮ ለልብየ፤
አመከርከነ ወኢተረክበ ዐመጻ በላዕሌየ፤
ከመ ኢይንብብ አፉየ ግብረ እጓለ እመሕያው፡፡

አማርኛ ፡-                


ልቤን ፈተንከው በሌሊትም ጎበኘኸኝ፤
ፈተንከኝ ምንም አላገኘህብኝም፤
የሰውን ሥራ አፌ እንዳይናገር ፈቃዴ ነው፡፡


ወንጌል:-           ዮሐ 3 ፥1-20
ቅዳሴ:-            ቅዳሴ ማርያም